1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ
ትምህርትአፍሪቃ

ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ-ራስ ገዝ የመሆን ጉዞ

መሳይ ተክሉ
ሐሙስ፣ ግንቦት 28 2017

የምርምር ዩኒቨርሲቲ ሆኖ የማገልገል ቀጣይ ተልዕኮ ከተሰጣቸው ስምንት ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ የሆነው ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ በቀጣዮቹ ዓመታት ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ሆኖ ለመሥራት የሚያስችለውን ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ዐሳውቋል ።

 ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ
ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ፤ የካንሰር ማዕከልምስል፦ Messay Teklu/DW

ሀረማያ አንጋፋ ከሚባሉ የሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ ነው

This browser does not support the audio element.

የምርምር ዩኒቨርሲቲ ሆኖ የማገልገል ቀጣይ ተልዕኮ ከተሰጣቸው ስምንት ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ የሆነው ሀረማያ ዩኒቨርሲቲበቀጣዮቹ ዓመታት ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ሆኖ ለመሥራት የሚያስችለውን ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ዐሳውቋል ።

 ወደ ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲነት ለሚደረገው ጉዞ አንዱ የራስን የፈይናንስ ምንጭ ማመንጨት መሆኑን የጠቀሱት ዶ/ር ኢስሀቅ በምርምር እና ሌሎች መስኮች በዚህ ረገድ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አስረድተዋል።

ለዶይቼ ቬለ አስተያየታቸውን የሰጡት የዩኒቨርሲቲው የምርምር እና ማህበረሰብ ጉድኝት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኢስሀቅ ዩሱፍ ዩኒቨርሲቲው ለምርምር የሚውለውን ሰባ አምስት በቶ ያህል የበጀት ምንጭ በራሱ ማመንጨት መጀመሩን ተናግረዋል።-

በሀገሪቱ በቀጣይ ተልዕኳቸው የምርምር ተቋማት ተብለው ከተለዩ ስምንት ያህል ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ የሆነው ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ በመንግስት የተሰጠውን ኃላፊነት ለመወጣት የተለያየ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው የምርምር እና ማህበረሰብ ጉድኝት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኢሳቅ ዩሱፍ ተናግረዋል።

አንጋፋ ከሚባሉ የሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ የሆነው ሀረማያ ከአራት ዐሥርተ ዓመታት በላይ የካበተ ልምድ ያካበተበት ግብር እና የጤናው ዘርፍ ቀጣይ ትኩረቶቹ መሆናቸው ተገልጿል ።

የተሰጠውን ተልዕኮ ከግብ ለማድረስ አሁን ያለውን የማህበረሰብ ብዛት እና ሌሎችነባራዊ ሁኔታዎች ትኩረት መስጠት አለበት ያሉት የዩኒቨርሲቲው ምክትል ቦርድ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር ኢማና ጌቱ ናቸው።

የሀረማያ ዩኒቨርሲቲው ምክትል ቦርድ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር ኢማና ጌቱምስል፦ Mesay Teklu/DW

ለዶይቼ ቬለ አስተያየታቸውን የሰጡት ፕሮፌሰር ኢማና ዩኒቨርሲቲው ዓላማውን ለማሳካት በቀጣይ ትኩረት ሊሰጥባቸው ይገባል ያሏቸውን ጉዳዮች አብራርተዋል።

በሌላ በኩል ዩኒቨርሲቲው ለአካባቢው ማኅበረሰብ በሚሰጣቸው የተለያዩ ድግፎች እና አገልግሎቶች ዙርያ የሚወያይበት እና በአመቱ የተሰሩ የምርምር ስራዎች የሚቀርብበትን መድረክ ዘንድሮ ለአርባ ሁለተኛ ጊዜ አካሂዷል ።

መሣይ ተክሉ

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ሸዋዬ ለገሠ

 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW