ሃገር በቀል የኤኮኖሚ ማሻሻያ መርሃ ግብር
ሐሙስ፣ ነሐሴ 23 2011![Äthiopien Addis Abeba Home grown economic reform Forum | Demeke Mekonnen](https://static.dw.com/image/50211426_800.webp)
ማስታወቂያ
ሃገር በቀል የኤኮኖሚ ማሻሻያ መርሃ ግብር
ፈጣን የሚባለው የኢትዮጵያ እድገት ዘላቂ እንዲሆን ለወጣቱም የተሻለ የሥራ እድል እንዲፈጠር ታስቦ የተዘጋጀው ሃገር በቀል የኤኮኖሚ ማሻሻያ መርሃ ግብር ትናንት አዲስ አበባ ውስጥ በተካሄደ ስብሰባ ይፋ ተደርጓል።በስብሰባው ላይ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ እንደተናገሩት የኤኮኖሚ ማሻሻያ መርሃ ግብሩ ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ኤኮኖሚ መገንባትንም ያካታታል። በዚሁ ስብሰባ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ባሰሙት ንግግር ባለፉት 15 ዓመታት በኢትዮጵያ በኤኮኖሚው ዘርፍ ተመዝግበዋል ካሏቸው በጎ ውጤቶች ጎን የፍትሃዊነት መጓደልና የማክሮ ኤኮኖሚ መዛባት ችግር እንደነበርም ገልጸዋል።በስብሰባው ላይ ልዩ ልዩ ምሁራን የግሉ ዘርፍ ተወካዮች እና ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል። የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ስብሰባውን ተከታትሏል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ኂሩት መለሰ
ተስፋለም ወልደየስ