1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ለመንግስት ሠራተኞች የተደረገው የደሞዝ ጭማሪ፣ ስጋቱና ዘላቂው መፍትሔ

እሑድ፣ ነሐሴ 25 2017

ጭማሪው ተግባራዊ እንዲደርግ ለዓመታት የታገሉ የሠራተኛና የሙያ ማኅበራት እንዲሁም ሌሎች አካላት ጥያቄአቸው መልስ በማግኘቱ መደሰታቸውን እየገለጹ ነው። ጭማሪው ሊያስከትል ይችላል የሚሉት የሸቀጦችና የሌሎች መሠረታዊ ፍላጎቶች የቤት ኪራይና የመሳሰሉት ዋጋ ንረት ያሳሰባቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች ማስተካከያው ትርጉም የለውም እያሉ ነው።

የኢትዮጵያ መንግሥት በአዲሱ ዓመት ከመስከረም 2018 ጀምሮ ፣ለመንግሥት ሠራተኞች ፣የደሞዝ ጭማሪ እንደሚያደርግ በቅርቡ አሳውቋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት በአዲሱ ዓመት ከመስከረም 2018 ጀምሮ ፣ለመንግሥት ሠራተኞች ፣የደሞዝ ጭማሪ እንደሚያደርግ በቅርቡ አሳውቋል። ምስል፦ Eshete Bekele/DW

ለመንግስት ሠራተኞች የተደረገው የደሞዝ ጭማሪ፣ ስጋቱና ዘላቂው መፍትሔ

This browser does not support the audio element.

የኢትዮጵያ መንግሥት በአዲሱ ዓመት ከመስከረም 2018 ጀምሮ ፣ለመንግሥት ሠራተኞች ፣የደሞዝ ጭማሪእንደሚያደርግ በቅርቡ አሳውቋል። መንግስት 160 ቢሊዮን ብር ወጪ እንደሚያደርግበት የገለጸው ይህ የደሞዝ ማስተካከያ የተለያዩ አስተያየቶች እየተሰነዘሩበት ነው።  ጭማሪው  ተግባራዊ እንዲደርግ ለዓመታት ሲወተውቱና ሲሞግቱ የቆዩ፣ የሠራተኛ እና የሙያ ማኅበራት እንዲሁም ሌሎች አካላት ጥያቄአቸው መልስ በማግኘቱ መደሰታቸውን እየገለጹ ነው።

በአንጻሩ ጭማሪው ሊያስከትል ይችላል የሚሉት የሸቀጦች እና የሌሎች መሠረታዊ ፍላጎቶች እንዲሁም የቤት ኪራይና የመሳሰሉት ዋጋ ንረት ያሳሰባቸው ሠራተኞችም ሆኑ ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች ማስተካከያው ትርጉም የለውም እስከማለት ደርሰዋል። መንግስት በበኩሉ በደመወዝ ማስተካከያው ሰበብ ዋጋ በሚጨምሩ ላይ ቁጥጥር እንደሚያደርግና ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።

 በሌላ በኩል ጭማሪው ያላካተታቸው በግል እና በመንግሥት የልማት ድርጅቶች የተሰማሩ ሠራተኞች የእኛስ ጉዳይ ሲሉ ጥያቄ እያቀረቡ ነው። የጭማሪው ፋይዳእና ስጋቶቹ እንዲሁም ለስጋቶች የሚሰጡ መፍትሔዎች የዛሬው እንወያይ የመነጋገሪያ ነጥቦች ናቸው።

ሠራተኞችም ሆኑ ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች ጭማሪው ሊያስከትል ይችላል የሚሉት የሸቀጦችና የሌሎች መሠረታዊ ፍላጎቶች ዋጋ ንረት ያሳሰባዋል።ምስል፦ Solomon Much/DW

 በዚህ ውይይት ላይ  አቶ ካሳሁን ፎሎ የኢትዮጵያ የሠራተኛ ማኅበራት ኮንፈደሬሽን ፕሬዝዳንት ፣ ዶክተር ዮሐንስ በንቲ የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ፕሬዝዳንት አቶ ሸዋፈራሁ ሽታሁን የፖለቲካዊ-ኤኮኖሚ  ጉዳዮች ተንታኝ እንዲሁም የዶቼቬለ ዘጋቢ ሰሎሞን ሙጬ ተሳትፈዋል። 

ሙሉውን ውይይት ለመከታተል ከታች የሚገኘውን የድምጽ ማዕቀፍ ይጫኑ 

ኂሩት መለሰ  

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ
ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW