1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ለጤና ሚኒስቴር የተደረገው የቁሳቁስ ድጋፍ

ሐሙስ፣ መጋቢት 30 2013

በምሥራቅ አፍሪካ በይነ መንግሥታት (IGAD) እና በአውሮጳ ሕብረት ኢትዮጵያ የኮሮና ተኅዋሲ ወረርሽኝን ለመግታት የምታደርገውን ጥረት የሚያግዝ የ60 ሚሊየን ብር ግምት ያለው  የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ።  የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጃ ዱጉማ ድጋፉ ጫናዎችን ለመቋቋም ይረዳል ብለዋል።

Äthiopien Konferenz COVID-19 in der IGAD-Region
ምስል፦ Seyoum Getu/DW

ኢጋድ እና የአውሮጳ ኅብረት ለኢትዮጵያ የጤና ቁሳቁስ ድጋፍ አድርገዋል

This browser does not support the audio element.

በምሥራቅ አፍሪካ በይነ መንግሥታት (IGAD) እና በአውሮጳ ሕብረት ኢትዮጵያ የኮሮና ተኅዋሲ ወረርሽኝን ለመግታት የምታደርገውን ጥረት የሚያግዝ የ60 ሚሊየን ብር ግምት ያለው የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ።  የተቋማቱ ባለሥልጣናት ዛሬ በአዲስ አበባ ለኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ድጋፉን ሲያስረክቡ ወረርሽኙ ሊያድርስ የሚችለውን ቀውስ ለመቋቋም መሰል ድጋፎችን ማድረግ  እንደሚቀጥሉም አስታውቀዋል፡፡
የኮሮና ተዋሲ ወረርሽኝ በሌሎች የጤና እክሎች ተደራሽነት ላይ የጎላ ተፅእኖን አሳርፏል ያሉት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጃ ዱጉማ ድጋፉ መሰል ጫናዎችን ለመቋቋም ይረዳል ብለዋል።
ስዩም ጌቱ 
ታምራት ዲንሳ
 ኂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW