1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሊቢያ እና ምክር ቤታዊው ምርጫ

ሰኞ፣ ሐምሌ 2 2004

ሊቢያውያን ሀገሪቱን ለአርባ ሁለት ዓመታት የገዙት የቀድሞው መሪ ሞአመር ኧል ጋዳፊ በሕዝብ ዓመፅ ከተወገዱ ወዲህ ባለፈው ቅዳሜ የብሔራዊ ምክር ቤት እንደራሴዎቻቸውን የመረጡ ሲሆን ፡ ሀገሪቱ ወደዴሞክራሲያዊው ሥርዓት ለመሸጋገር በያዘችው ሂደት ላይ ይህ የመጀመሪያው ርምጃ ሆኖ አግኝተውታል፤

High National Election Commission workers check ballot boxes after collecting them from different polling stations as they prepare for the final count, in Benghazi July 8, 2012. Nine months after Muammar Gaddafi's death at the hands of rebels, Libya has defied fears it would descend into violence by pulling off a largely peaceful election, its first national and free vote in 60 years. REUTERS/Esam Al-Fetori (LIBYA - Tags: POLITICS ELECTIONS)
ምስል Reuters

ይሁንና፡ ይኸው የመጀመሪያ ነፃ የምርጫ ሂደት በሀገሪቱ በቀጠለው የጎሳ ግጭትና ሕዝብ ከምርጫ እንዲርቅ በቀረበ ጥሪ ጥላ አጥሎበታል። ለሞአመር በአርባ ዓመቱ የጋዳፊ አመራር ዘመን ምክር ቤትም ሆነ ሕገ መንግሥት አልነበረም። የፖለቲካ ፓርቲ ምሥረታምም ሆነ አባልነት በሞት ያስቀጣም ነበር። ዎች ጋዳፊ ከተገደሉ ከዘጠኝ ወራት በኋላ ሊቢያውያን ድምፃቸውን እንዲሰጡ መጠራታቸውን እንደ አዲስ ክስተት ነው የተመለከቱት። የመምረጥ መብት ያላቸው 2,8 ሚልየን ሊቢያውያን ሁለት መቶ መንበሮች ለሚኖሩት ምክር ቤት በተፎካካሪነት ከቀረቡ 3,800 ዕጩዎች እና ከ 140 ፓርቲዎች መካከል መምረጥ ይችላሉ። ግን በሀገሪቱ ዴሞክራሲያው ባህል ባለመኖሩ፡ ለብዙ መራጮች ድምፅ በሚሰጡበት ውሳኔአቸው ላይ ተወዳዳሪ ዕጩዎች ከየትኛው አካባቢ ወይም ጎሳ መጡ የሚለው ጉዳይ እንጂ የሚከተሉት የፖለቲካ ፕሮግራማቸው ትርጉም እንደሌለው የሊቢያን ፖለቲካ በቅርብ የሚከታተሉ የፖለቲካ ተንታኞች ገልጸዋል።
አዲስ የሚመረጠው ብሔራዊ ምክር ቤት ሀገሪቱን በጊዚያዊነት የሚያስተዳድር የሽግግር መንግሥት ያቋቁማል፤ ሕገ መንግሥታዊውን ምክር ቤትም ይሠይማል። ከዚያ መራጩ ሕዝብ ወደፊት በሚካሄደው ሁለተኛ ምርጫ በሚረቀቀው ሕገ መንግሥት ላይ ድምፁን ይሰጣል ። በነዳጅ ዘይት የተፈጥሮ ሀብት ለታደለችውና በአምባገነን ሥርዓት ሥር ለቆየችው ሰሜን አፍሪቃዊቱ ሀገር ልትወጣው የምትገባ ትልቅ ፈታኝ ሁኔታ ነው። ሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች በተቀናቃኝ ቡድኖች፡ ባማፅያን ሚሊሺያዎችና በጎሳዎች መካከል በሚካሄዱ ግጭቶች አሁንም አሳሳቢ ችግር የተደቀነባት ሲሆን፡ በምሥራቃዊው የሀገሪቱ ከፊል የሚንቀሳቀሱ አንዳንድ ኃይላት ሕዝቡ በዛሬው የብሔራዊ ምክር ቤት ምርጫ እንዳይሳተፍ የተጠናከረ ጥሪ ሲያስተላልፉ ነው የቆዩት። ሊቢያን በወቅቱ የሚያስተዳድረው የሽግግሩ ምክር ቤት የፀጥታው ጥበቃ ከቁጥጥር እንዳይወጣ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ቢገኝም፡ በብዙ የሀገሪቱ አካባቢዎች አሁንም ከባድ ውጊያ እንዳለ ነው የሚሰማው፤ በተለይ ብዙ የጦር መሣሪያ የሚዘዋወርበት ድርጊት ሁኔታውን አዳጋች አድርጎታል።
አርያም ተክሌ

ምስል picture-alliance/dpa

መሥፍን መኮንን

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW