ላምሮት ከማል በዋስ እንድትለቀቅ ተወሰነ
ሐሙስ፣ ኅዳር 9 2014ማስታወቂያ
ድምፃዊ ሐጫሉ ሁንዴደሳን በመግደል ወይም በማስገደል በአራተኛ ተጠርጣሪነት ተከስሳ የነበረችዉ ላምሮት ከማል በዋስ እንድትፈታ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወሰነ። አቃቤ ሕግ በላምሮት ላይ ለመሰረተዉ የአሸባሪነት ክስ በቂ መረጃ አላገኘንም ያሉት የፌደራሉ ከፍተኛና ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ከዚሕ ቀደም ክሱን ዉድቅ አድርገዉት ነበር። የአቃቤ ሕግና የተከሳሽ ጠበቆች ክርክር በስር ፍርድ ቤት ቀጥሎ ዛሬ አዲስ አበባ ያስቻለዉ ፍርድ ቤት ተከሳሽዋ በ5ሺሕ ብር ዋስ ተለቅቃ እንድትከራከር በይኗል።
ስዩም ጌቱ
ነጋሽ መሐመድ
ኂሩት መለሰ