1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

«ሕወሓት ከአዲስ አበባ ሌላ ጉዳይ የለውም» ጌታቸው ረዳ

ሰኞ፣ ጥቅምት 29 2014

በትግራይ ክልል ላይ የተጣሉ ዕቀባዎች ከተነሱ እና  የተቋረጡ አገልግሎቶች ከተመለሱ ሕወሓት የተኩስ አቁም ለማድረግ እና ለመደራደር ፍቃደኛ መሆኑን የግንባሩ  ቃል አቃባይ ጌታቸው ረዳ ተናገሩ ። ቃል አቃባዩ ዛሬ ከዶይቼ ቬለ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ «ሕወሓት ከአዲስ አበባ ሌላ ጉዳይ የለውም» ብለዋል።

Äthiopien Getachew Reda in Addis Abeba
ምስል DW/Y. Geberegeziabeher

የሕዝባዊ ወያነ አርነት ትግራይ ሕወሓት ቃል አቃባይ ጌታቸው ረዳ ሙሉ ቃለ ምልልስ

This browser does not support the audio element.

በትግራይ ክልል ላይ የተጣሉ ዕቀባዎች ከተነሱ እና  የተቋረጡ አገልግሎቶች ከተመለሱ ሕወሓት የተኩስ አቁም ለማድረግ እና ለመደራደር ፍቃደኛ መሆኑን የግንባሩ  ቃል አቃባይ ጌታቸው ረዳ ተናገሩ ። ቃል አቃባዩ ዛሬ ከዶይቼ ቬለ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ «ሕወሓት ከአዲስ አበባ ሌላ ጉዳይ የለውም» ብለዋል።
በአፍሪቃ ቀንድ የአፍሪቃ ሕብረት ልዩ ልዑክ ኦሊሴንጎ ኦባሳንጆ ከሕወሓት ሊቀመንበር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ጋር ተገናኝተው መነጋገራቸውን ያነሱት አቶ ጌታቸው ፤ የንግግሩ ይዘት  በሂደት ያለ በመሆኑ ዝርዝር ጉዳዮችን ከመግለጽ ተቆጥበዋል። 
የሕወሃት ቃል አቃባይ ጌታቸው ረዳ ድርጅታቸዉ ይፈፅማቸዋል ስለተባሉ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች፣ ከሕዝብ ስለሚደርስበት ተቃዉሞ፣ ከዩናይትድ ስቴትስ ይሰጠዋል ስለሚባለዉ ድጋፍ፣ ከሌሎች ስምንት ቡድናት ጋር ስለመሰረተዉ ትብብር እና በተያያዥ ጉዳዮች ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች መልስ ሰጥተዋል።
 ነጋሽ መሐመድ አነጋግሯቸዋል። 
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW