1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሕገወጥ የደን ወረራ በደቡብ ክልል

ሐሙስ፣ ጥር 2 2011

በደቡብ ክልል የተከሰተውን የፀጥታ ችግር ተከትሎ እየተስፋፋ መጣው ሕገወጥ የደን ወረራ አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱ እየነገረ ነው ፡፡ በክልሉ የከፋ ዞን የአካባቢ ጥበቃና ደን ጽሕፈት ቤት እንዳስታወቀው ካለፈው የሰኔ ወር አንስቶ በዞኑ በሚገኙ ስምንት ወረዳዎች ውስጥ ሃያ አምስት ሺህ ሄክታር የሚሸፍን የደን ይዞታ በሕገወጦች ተወስዷል፡፡

Wald in Süd Äthiopien,
ምስል DW/ Shewangizaw W

«የከፋ ዞን ጥብቅ የተፈጥሮ ደን በተፈጥሯዊ መስህብነት በዩኔስኮ ተመዝግቧል»

This browser does not support the audio element.

 የደቡብ ክልል የአካባቢ፤ ደንና የአየር ንብረት ለውጥ ቁጥጥር የሥራ ኃላፊዎች በበኩላቸው በተፈጥሮ ደኑ ላይ እየተካሄደ የሚገኘወን ወረራ ለመከላከል ወራሪዎቹን የመለየት እና ከደኑ ይዞታ የማስወጣት ሥራ መጀመሩን እየተናገሩ ነው፡፡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ባለፉት ግማሽ ምዕተ ዓመት የኢትዮጵያ የደን ሽፋን በከፍተኛ ሁኔታ እያሽቆለቆለ ይገኛል፡፡
በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ከሚገኙት ጥቂት የደን ቅሪቶች መከከል እንዱ ጥቅጥቅ ባሉ አገር በቀል ዛፎች የተሸፈነው የከፋ የተፈጥሮ ደን ይገኝበታል፡፡  ይሁንእንጂ ይህ የተፈጥሮ ደን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በክልሉ የተከሰተውን የፀጥታ ችግር ተከትሎ ህልውናው በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ መውደቁ እየተነገረ ይገኛል ፡፡ የከፋ ዞን የአካባቢ ጥበቃና ደን ጽሕፈት ቤት እንዳስታወቀው የከፋ የተፈጥሮ ደን ካለፈው የሰኔ ወር አንስቶ በሕገወጥ ግለሰቦችና ቡድኖች እየተወረረ ይገኛል ፡፡ እስከአሁንም የተፈጥሮ ሀብቱ በሚገኝባቸው ስምንት ወረዳዎች ውስጥ ሃያ አምስት ሺህ ሺህ ሄክታር የሚሸፍን የደኑ ይዞታ በሕገወጦች መወሰዱን በጽሕፈት ቤቱ የደን ልማትና ጥበቃ ዋና ሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ኢያሱ ወልደጊዮርጊስ ለዲ ደብሊው ገልጸዋል፡፡

አቶ ኢያሱ ወልደ ጊዮርጊስ

የከፋ ዞን ጥብቅ የተፈጥሮ ደን የአካባቢውን የአየር ሚዛን ከመጠበቁም በተጨማሪ ባለው ተፈጥሯዊ መስህብነት የተነሳ በዩኔስኮ ተመዝግቦ ይገኛል የሚሉት አቶ እያሱ አሁን የሚታየው ወረራ ከወዲሁ ካልተገታ በቀጣይ አለምአቀፍ ዕውቅናውን ሊነጠቅ ይችላል የሚል ሥጋት እንዳላቸውም ጠቅሰዋል፡፡ ዲ ደብሊው በጉዳዩ ላይ ያነጋገራቸው የደቡብ ክልል የአካባቢ፤ ደንና የአየር ንብረት ለውጥ ቁጥጥር ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳሙኤል ቀቀቦ በበኩላቸው በከፋ ዞን የተፈጥሮ ደን ላይ ህገ ወጥ ወረራ መካሄዱን አረጋግጠዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ባለሥልጣን መሥሪያቤቱ ከተለያዩ አካላት ጋር በመቀናጀት ህገ ወጥ ወራሪዎቹን የመለየት እና ከደኑ ይዞታው የማስወጣት ሥራ መጀመሩን ተናግረዋል፡፡ የሀዋሳው ወኪላችን ሸዋንግዛው ወጋየሁ ዝርዝሩን ልኮልናል።

ሸዋንግዛው ወጋየሁ

ሸዋዬ ለገሠ

አርያም ተክሌ

 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW