1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

መቀሌ በግጭት ማግሥት

ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 15 2013

በመቀሌ ስልክ፣ ሆስፒታሎች፣ ጤና ጣቢያዎች፣ የመድሐኒት መደብሮችና ታክሲዎች ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል አገልግሎት እየሰጡ ነው። ነዳጅ ማደያዎች፣ ባንኮችና አብዛኞቹ ሱቆች ግን አሁንም ዝግ ናቸው። ፖሊስ ጣቢዎችና ፍርድ ቤቶችም ዝግ ናቸው። ለአንድ ወር ያሕል መዘገብ አቋርጦ የነበረዉ የመቀሌው ወኪላችን ሚሊዮን ኃይለ ስላሴም ዛሬ ሥራ ጀምሯል

Äthiopien Tigray | Hauptstadt Mekele
ምስል Edwin Remsberg/imago images

  መቀሌ በግጭት ማግሥት

This browser does not support the audio element.

ላለፉት ሁለት ወራት ግድም ተዋጊ ጄትና ሄሊኮብተርና የጦር አዉሮፕላኖች ሲያጉረመርሙበት የነበረዉ የመቀለ ሰማይ ዛሬ የመንገደኞች አዉሮፕላን ድምፅ ተሰምቶበታል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ52 ቀናት በፊት አቋርጦት የነበረዉን የከና ወደ መቀሌ በረራ ዛሬ ጀምሯል። የትግራይ ርዕሠ-ከተማ አጠቃላይ እንቅስቃሴም እየተረጋጋ ነው። ስልክ፣ ሆስፒታሎች፣ ጤና ጣቢያዎች፣ የመድሐኒት መደብሮችና ታክሲዎች ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል አገልግሎት እየሰጡ ነው። ሸቀጥም ወደ ከተማይቱ እየገባ ነው። ነዳጅ ማደያዎች፣ ባንኮችና አብዛኞቹ ሱቆች ግን አሁንም ዝግ ናቸው። ፖሊስ ጣቢዎችና ፍርድ ቤቶችም ዝግ ናቸው። ለአንድ ወር ያሕል መዘገብ አቋርጦ የነበረዉ የመቀሌው ወኪላችን ሚሊዮን ኃይለ ስላሴም ዛሬ ሥራ ጀምሯል። በስልክ አነጋግሬዋለሁ።

ሚሊዮን ኃይለስላሴ

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሠ
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW