1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

መቐለን ጨምሮ በትግራይ ከተሞች የተስፋፋዉ ወንጀል አሳሳቢ ሆንዋል ተባለ

ሚሊዮን ኃይለ-ሥላሴ
ሰኞ፣ ነሐሴ 12 2017

በመቐለ ጨምሮ በተለያዩ የትግራይ ከተሞች በተደጋጋሚ የሚፈፀሙ ወንጀሎች የኅብረተሰብ የደኅንነት ስጋት ሆነው እንዳለ ተገለፀ። ነዋሪዎች ግድያ፣ እገታ እና ዝርፍያ ጨምሮ ሌሎች ወንጀሎች እየተፈፀሙ መሆኑ ይናገራሉ። የክልሉ ፖሊስ ኮምሽን እነዚህ ሕብረተሰብ ያማረሩ የወንጀል ተግባራት እየተፈፀሙ መሆኑ በማመን፥ እርምጃዎች እየወሰደ መሆኑ ይገልፃል።

ምስል ከማህደር፤ የህወሓት ወታደር በሃዉዜን 2021
ምስል ከማህደር፤ የህወሓት ወታደር በሃዉዜን 2021 ምስል፦ Ben Curtis/AP/picture alliance

መቐለን ጨምሮ በትግራይ ከተሞች የተስፋፋዉ ወንጀል አሳሳቢ ሆንዋል ተባለ

This browser does not support the audio element.

 

በትግራይ በተለይም ከጦርነቱ በኃላ በከተሞች በርካታ ወንጀሎች እየተፈፀሙ መሆኑ በነዋሪዎች የሚገለፅ ሲሆን በነዚህ ወንጀሎች በርካቶች ሞተዋል፣ እገታ እና ዝርፍ መበራከቱ ይገለፃል። በዚህ ሳምንት እንኳን በመቐለ ከስራው ወደቤቱ ሲመለስ የነበረው ወጣት ድንገት መጥፋቱ በበርካቶች ዘንድ ቁጣ እንዲሁም ስጋት የፈጠረ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም የአክሱም ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህር እና ተመራማሪ በድንገተኛ ሁኔታ መገደላቸው ተነግሯል። እነዚህ ወንጀሎች በፖሊስ ክትትል እየተደረገባቸው ላይ መሆናቸው ተገልጿል። 

ከዚህ በተጨማሪ በትግራይ የተለያዩ ከተሞች በህፃናት እና ሴቶች ጨምሮ በበርካቶች ላይ ዝርፍያ እና ፆታዊ ጥቃት ዓለማ ያደረጉ በርካታ ወንጀሎች ይፈፀማሉ። እነዚህ ወንጀሎች ነዋሪዎች አማረው ይገኛሉ።  በትግራይ የጋዜጠኞች መታገት

በክልሉ በአጠቃላይ በተለይም ደግሞ በትላልቅ ከተሞች በትጥቅና እና ተሽከርካሪዎች የተደገፈ ዝርፍያ፣ በህፃናት እና ሴቶች ጨምሮ በተለያዩ ነዋሪዎች የሚፈፀም እገታ ብሎም ግድያ፣ ሕገወጥ የሰዎች ዝውውር እንዲሁም ሌሎች እየተፈፀሙ እንዳለ የክልሉ አስተዳደር ጭምር ይገልፃል። በቅርቡ በድንገት በሚደረጉ ፍተሻዎች ሕገወጥ የጦር መሳርያዎች፣ ለወንጀል ተግባራት የሚውሉ ስለቶች እና ሌሎች መሳርያዎች መያዙ የሚገልፀው የትግራይ ፖሊስ ኮምሽን ወንጀሎች ለመከላከል እየሰራ ቢሆንም አሁንም ግድያ ጨምሮ ሌሎች ተግባራት መቀጠላቸው ይገልፃል። የትግራይ ፖሊስ ኮምሽን ምክትል ኮምሽነር ጌታቸው ኪሮስወንጀል ለመከላከል እየሰራን ቢሆንም አሁንም ግድያ አለ፣ የግድያ ሙከራ ይፈፀማል፣ ንጥቅያ አለ። ወንጀል ሙሉበሙሉ ማስቆም ባይቻልም ስጋት የሚያስወገድ ማድረግ ይገባል። ህዝብ በሰላም ወጥቶ እንዲገባ መስራይ ይጠበቅብናል" ብለዋል። በቅርቡ የሚከበሩ በዓላት ተከትሎ እንግዶች ወደመቐለ በብዛት ይመጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የተናገሩት የፖሊስ አዛዡ ጥበቃ ይደረጋል ስጋት አይግባችሁ ሲሉ ተደምጠዋል።

 

ሚሊዮን ኃይለሥላሴ

አዜብ ታደሰ

ታምራት ዲንሳ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW