መተከል ዞን ታጣቂዎች ሰዉ ገደሉ
ረቡዕ፣ ኅዳር 1 2014ማስታወቂያ
በበኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ድባጤ ወረዳ የሸመቁ ታጣቂዎች ባለፈዉ ሰኞ በከፈቱት ተኩስ 4, ሰዎች ገደሉ።ሌሎች 6 ሰዎች አቆሰሉ።ትናንት በዜና እንደዘገብነዉ ታጣቂዎቹ ሰላማዊ ሰዎችን ከመግደል፣ ማቁሰላቸዉ በተጨማሪ የአካባቢዉን ገበሬዎች የቀንድ ከብቶች ዘርፈዋልም።የአሶሳዉ ወኪላችን ነጋሳ ደሳለኝ ያነጋገራቸዉ የወረዳዉ ነዋሪዎች እንደገለፁት የመከላከያ ሠራዊትና ከተለያዩ ክልሎች የዘመቱ ሚሊሺያዎች የመተከል ዞንን ፀጥታ እየተቆጣጠሩ ቢሆንም ታጣቂዎች ሰላማዊ ሰዎችን መግደል፣ ማቁሰልና መዝረፋቸዉ እንደቀጠለ ነዉ።
ነጋሳ ደሳለኝ
ነጋሽ መሐመድ
አዜብ ታደሰ