መኢአድ የታሰሩት አባላቱ በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጠየቀ
ማክሰኞ፣ ጥር 16 2009ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ «የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት» በምህጻሩ መኢአድ በደቡብ ክልል ሰሞኑን የታሰሩት አባላቱ በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጠየቀ ። የመኢአድ ሊቀመንበር ለዶቼቬለ በሰጡት ቃለ ምልልስ እንደተናገሩት በደቡብ ኦሞ ጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ ፓሊስ ጣቢያ ውስጥ ከቅዳሜ አንስቶ የታሰሩት የመኢአድ 3 አመራሮችን ጨምሮ 13 አባላቱ እንዲፈቱ ፓርቲያቸው ለአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ኮማንድ ፖስት በጽሁፍ ጥያቄውን አቅርቧል ። መኢአድ እንደሚለው የታሰሩት ሦስቱ አመራሮች የፓርቲው የደቡብ ቀጣና ተጠሪዎቹ ናቸው ። ሰዎቹ በቁጥጥር ስር ይገኙበታል የተባለውን የሳውላ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ ሃላፊዎች ለማነጋገር የአዲስ አበባው ወኪላችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ያደረገው ሙከራ አልተሳካም ።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ