1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

መድረክ ከኢህአዴግ ጋር የሁለትዮሽ ዉይይትን ጠየቀ

ዓርብ፣ መጋቢት 22 2009

ኢህአዴግ ከመድረክ ጋር የሁለትዮሽ ድርድር በአስቸኳይ እንዲጀምር መድረክ አሳሰበ። ለሃገራችን ፖለቲካዊ ችግሮች ትክክለኛ መፍትሄ ለማግኘት ኢህአዴግ ከሃቀኛ ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ድርድር ሊያካሂድ ይገባል፤ ይላል መድረክ ዛሬ ባስነበበዉ የጽሑፍ መግለጫ ርዕስ። ፓርቲዉ ሊደራደርባቸዉ የሚያስፈልጉ አስቸኳይ ጉዳዮች አሉም ብሎአል።

Äthiopien Pressekonferenz
ምስል DW/G. Tedla

Ber. A.A (MEDREK will nur bilaterale Verhandlungen mit EPRDF) - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.

የመድረክ የወቅቱ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስን ጨምሮ የመድረክ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ዛሬ ከቀትር በኋላ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ መድረክ ላቀረባቸዉ ጥያቄዎች ፈጣንና ተጨባጭ ዉጤቶችን ሊያስገኝ የሚችለዉ የሁለትዮሽ ድርድር ሲካሄድ ነዉ ብለዋል።  


ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር


አዜብ ታደሰ

ሸዋዬ ለገሠ
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW