1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሙርሲና የቀጠለው ተቃውሞ

ሰኞ፣ ኅዳር 17 2005

የግብፅ አስተዳደራዊ ጉዳዮች ፍርድ ቤት የፕሬዝዳንቱ ድንጋጌ እንዲሻር የቀረቡትን ክሶች በሚቀጥለው ሳምንት እንደሚመረምር አስታውቋል ። የግብፅ ዜና አግልግሎት ሜና እንደዘገበው ከ12 የሚበልጡ ተመሳሳይ ክሶች ቀርበዋል ።

Protesters throw branches on a bone fire as they clash with Egyptian riot policemen at Simon Bolivar square on November 25, 2012 in Cairo. Egypt's powerful Muslim Brotherhood called nationwide demonstrations today in support of Islamist President Mohamed Morsi in his showdown with the judges over the path to a new constitution. AFP PHOTO / GIANLUIGI GUERCIA (Photo credit should read GIANLUIGI GUERCIA/AFP/Getty Images)
ምስል Getty Images/AFP

የግብፁን ፕሬዝዳንት ሞሐመድ ሞርሲን ድንጋጌ በመቃውም በተካሄዱ ሰልፎች የተገደሉት 2 ግብፃውያን የቀብር ስነ ስርዓት በሺዎች የሚቆጠሩ ግብፃውያን በተገኙበት ዛሬ ተፈፀመ ። በስነ ስርዓቱ ላይ ከፊሉ ሲያነባ ከፊሉ ደግሞ የፍትህ ጥያቄ ሲቀርብ ተሰምቷል ። ዳማንሆር በተካሄደው በአንደኛው የቀብር ስርዓት ላይ የሞርሲ ደጋፊዎችና ተቃዋሚዎች ተጋጭተዋል ። ካለፈው ሳምንት አንስቶ በሞርሲ ደጋፊዎችና ተቃዋሚዎች መካከል በተካሄደው ግጭት 444 ሰዎች መቁሰላቸው ተዘግቧል ። በምርጫ የግብፅ ፕሬዝዳንት የሆኑት የሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲው ሞሐመድ ሙርሲ ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ሥልጣናቸውና ውሳኔያቸው አንዳችም ህጋዊ ተቃውሞ ሊቀርብበት እንደማይችል ከደነገጉ በኋላ ነበር ህዝቡ ተቃውሞውን ማሰማት የጀመረው ። ፕሬዝዳንት በዚሁ ድንጋጌ ላይ ከሃገሪቱ ከፍተኛ ዳኞች ጋር ይነጋገራሉ ተብሎ ይጠበቃል ። ዘግይቶ በደረሰን ዜና መሰረት የግብፅ አስተዳደራዊ ጉዳዮች ፍርድ ቤት የፕሬዝዳንቱ ድንጋጌ እንዲሻር የቀረቡትን ክሶች በሚቀጥለው ሳምንት እንደሚመረምር አስታውቋል ። የግብፅ ዜና አግልግሎት ሜና እንደዘገበው ከ12 የሚበልጡ ተመሳሳይ ክሶች ቀርበዋል ።

ምስል AP

ሒሩት መለሰ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW