1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ከሜጀር ጄነራል ክንፈ ጋር 7 ተጠርጣሪዎች ችሎት ቀርበዋል

ረቡዕ፣ ኅዳር 5 2011

የብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄነራል ክንፈ ዳኘው ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርቡ። ጄነራሉ ጠበቃ የማቆም አቅም እንደሌላቸው ለጊዜ ቀጠሮ ችሎት በመናገራቸው ፍርድ ቤቱ መንግስት ጠበቃ እንዲያቆምላቸው ወስኗል።

Police have detained Major General Kinfe Dagnew, former Director General of the state-owned Metals and Engineering Corporation
ምስል Ethiopian government communication

ከሜጀር ጄነራል ክንፈ ጋር ሰባት ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀርበዋል

This browser does not support the audio element.

በሁመራ በኩል ከሀገር ሊወጡ ሲሉ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ የተነገረላቸው እና ትላንት ወደ አዲስ አበባ እንዲመጡ የተደረጉት የብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄነራል ክንፈ ዳኘው ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። ከእርሳቸው ጋር የኢትዮ ቴሌኮም የስራ ኃላፊ የነበሩት ወንድማቸው ኢሳይያስ ዳኘው እና የቀድሞ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋዜጠኛ ፍጹም የሺጥላን ጨምሮ በድምሩ ስምንት ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

ዘገባውን ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ። 

 

ዩሃንስ ገብረ እግዚያብሔር 

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW