ከሜጀር ጄነራል ክንፈ ጋር 7 ተጠርጣሪዎች ችሎት ቀርበዋል
ረቡዕ፣ ኅዳር 5 2011![Police have detained Major General Kinfe Dagnew, former Director General of the state-owned Metals and Engineering Corporation](https://static.dw.com/image/46279909_800.webp)
ማስታወቂያ
በሁመራ በኩል ከሀገር ሊወጡ ሲሉ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ የተነገረላቸው እና ትላንት ወደ አዲስ አበባ እንዲመጡ የተደረጉት የብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄነራል ክንፈ ዳኘው ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። ከእርሳቸው ጋር የኢትዮ ቴሌኮም የስራ ኃላፊ የነበሩት ወንድማቸው ኢሳይያስ ዳኘው እና የቀድሞ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋዜጠኛ ፍጹም የሺጥላን ጨምሮ በድምሩ ስምንት ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀርበዋል።
ዘገባውን ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ።
ዩሃንስ ገብረ እግዚያብሔር
ነጋሽ መሐመድ