1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ምስራቅ ሊቢያ በቦንብ ተደበደበች

ማክሰኞ፣ መጋቢት 6 2003

ምስራቃዊ ሊቢያ ውስጥ ሰኞ መጋቢት 5 ቀን 2003 ዓ.ም. የመንግስት ወታደሮች አስጃዲያ የተሰኘችውን ከተማ በቦንብ መደብደባቸው ተዘገበ። እንደ አይን እማኞች ከሆነ፤ በቦንቡ ጥቃት አንድ ሆስፒታልና የከተማው ውሃ ማጠራቀሚያ ጋን ሲመታ በርካታ ሰላማዊ ሰዎች መሞታቸውና መቁሰላቸው ተገላጿል።

የሊቢያ አማፂያን በታንክ ላይ
የሊቢያ አማፂያን በታንክ ላይምስል dapd

ተቃማሚዎች በሊቢያ መንግስት የሚደርሰውን የአየር ጥቃት ለማስቆም ዓለም አቀፉ ማኅበረ-ሰብ ሊቢያ ላይ የበረራ እገዳ እንዲጥል ተማፅነዋል። በአንጻሩ የሊቢያ መንግስት ቻይናና ሩሲያን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራትን ለመዋዕል-ንዋይ ፍሰት በማግባባት ላይ መሆኑ ተጠቅሷል። ቻይናና ሩሲያ ድምፅን በድምፅ የመሻር መብት እንዳላቸው የሚታወቅ ነው። የሊቢያን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ማንተጋፍቶት ስለሺ የሚከተለውን አጠናቅሯል።

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW