ምክር ቤታዊ ምርጫ በኒዠር
ማክሰኞ፣ ጥቅምት 10 2002ማስታወቂያ
ድምጹን ለመስጠት የወጣው ህዝብ ቁጥር ያን ያህል ከፍተኛ አለመሆኑን የዜና ምንጮች ዘገባዎች አስታውቀዋል። የተቃውሞው ወገን ምርጫው ፕሬዚደንት ማማዱ ታንዣን ህገ መንግስቱ ከሚፈቅውደው የአስር ዓመት የስልጣን ዘመን በላይ ለማቆየት የታለመ ነው በሚል ህዝቡ ከድምጽ አሰጣጡ ስርዓት እንዲርቅ ቀደም ሲል ጥሪ ማቅረቡ ይታወሳል። የኒዠር ፕሬዚደንት ምርጫው ወደሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በተደጋጋሚ ያሰማውን ጥሪ ችላ በማለታቸው በምህጻሩ ኤኮዋስ የምዕራብ አፍሪቃ መንግስታት የኤኮኖሚ ማህበር ሀገሪቱን ከድርጅቱ ለጊዜው አግልሎዋል።
ጌታቸው ተድላ/አርያም ተክሌ/ሸዋዜ ለገሰ