1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ምዕራብ ወለጋ ዞን በዚህ ሳምንት አራት ሰዎች ተገደሉ

ነጋሣ ደሳለኝ
ረቡዕ፣ ጥር 21 2017

በምዕራብ ወለጋ ዞን 2 ወረዳ ውስጥ ከለፈው ቅዳሜ አንስቶ እስከ ትናንት ድረስ የ4 ሰዎች ህይወት ማለፉን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ ግዲያው በዞኑ ባቦ ጋምቤል ወረዳና ቅልቱ ካራ በተባሉ ወረዳዎች በጸጥታ ሐይሎች መፈጸሙንም አመልክተዋል፡፡ የባቦ ጋምቤል ወረዳ አስተዳዳሪ የመንግስት ጸጥታ ሀይሎች ግዲያውን ፈጽመዋል መባሉን አስተባብለዋል።

Äthiopien I West Wollega - Gimbi Stadt
ምስል፦ Negassa Dessalegn/DW

ምዕራብ ወለጋ ዞን በዚህ ሳምንት አራት ሰዎች ተገደሉ

This browser does not support the audio element.

በምዕራብ ወለጋ ሁለት ወረዳዎች የ4 ሰዎች ሕይወት አልፏል።


ለዓመታት በግጭት ውስጥ ከቆየው የምዕራብ ኦሮሚያ ዞኖች መካከል ምዕራብ ወለጋ ውስጥ የሚከሰቱት ጸጥታ ችግሮች የነዋሪውን እንቅስቃሴ መገደብን ጨምሮ በጤና ተቋማት ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ ማሳደሩን የአካባቢው ነዋሪዎች እና የጤና ባለሙያዎች ሲናገሩ ቆይተዋል፡፡ በዚህ አካባቢ በጸጥታ ሀይሎች እና ሸማቂዎች መካከል ግጭት በተለያየ ወቅቶች እንደሚሰከቱና በግጭት ውስጥ ያልተሳተፉ ሰላማዊ ሰዎች ላይ ጉዳት እየደረሰ እንደሚገኙ ያነጋገርናቸው ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ በዞኑ ባቦ ጋምቤል ወረዳ ደግሞ ጴጥሮሰ ፍቅሩ የተባሉና ሌላው አንድ ሰላማዊ  ነዋሪ ሰሞኑን ከታጣቂዎች ጋር ግንኙት አላችሁ በማለት በጸጥታ ሐይሎች ተይዘው መገደላቸውን አንድ የበተሰባቸው አባል ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም አሊይ የተባሉ የወረዳው ነዋሪው እንደዚሁ ከታጣቂዎች ጋር ግንኙነት አላህ በማለት በትናንትናው ዕለት በደረሰበት ድብደባ ከፍተኛ ጉዳት  እንደደረሰበት ጠቁመዋል፡፡

ምዕራብ ወለጋ አንዳንድ ወረዳዎች ኤሌክትሪክ እንደተቋረጠ ነው

‹‹ አሊይ ያደታ የተባለ በባቦ ጋምቤል ፖሊስ ጣቢያ ከታሰረ በኃላ ብዙ ጊዜ ድብደባ ተፈጽሞበት ተጎድ አሁን መናገር አይችልም፡፡ መልካ ኤቢቻ በተባለ ቦታ ደግሞ ጴጥሮስ ፍቅሩ የተባለ አንድ ሰው ተይዘው ተገድለዋል፡፡ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ትቀልባለህ ፣ትደግፍለህ በማለት  ነው የተገደለው፡፡ ሰው በጸጥታ ችግርም በጤና በኩልም እየተቸገረ ነው፡፡›› በማለት በአካባቢው የጸጥታ ችግር እያሳደረ ያለውን ተጽህኖ አብራርተዋል፡፡  በዚህ ጉዳይም ላይ መረጃ እንዲሰጡን የጠቅናቸው የባቦ ጋምቤል ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ በንቲ ቶሊና በጸጥታ ሐይሎች  በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል መባሉን እና ሰው ህይወት ማለፉን ካስተባበሉ በኃላ ጉዳዩን እንደገና ማጣራት እንዳለባቸው እና ከቀኑ ሰባት ሰዓት እንዲደውልላቸው በመናገር ስልካቸውን ዘግተዋል፡፡ በተባለው ሰዓት መልሰን ብንደወልላቸውም ሰልካቸው ዝግ ነው፡፡  

ምዕራብ ወለጋ ቀደም ሲልም ተደጋጋሚ ጥቃቶች ተከስተዋል ።ምስል፦ Negassa Dessalegn/DW

በዞኑ ቅልቱ ካራ ወረዳ ባለፈው ቅዳሜ የሰው ሕይወት አልፏል

በምዕራብ ወለጋ ዞን ቅልቱ ካራ ወረዳ ደግሞ ባለፈው ቅዳሜ ጠዋት 2 ፡00 ሰዓት ገደማ ወደ 3 ሰዎች ተዘይዘው በአካባቢው የሚንቀሳቀሰውን ታጣቂዎችን ደግፋቹሀል በሚል  2ቱ ሲገደሉ አንድ ሰው ደግሞ በደረሰበት ድብደባ  በመጎዳት  የህክምና እርዳታ እየሰተደረገለት እንደሚገኝ ያነጋርናቸው የአካባቢው ነዋሪዎች አመልክተዋል፡፡  « ቅዳሜ ጠዋት  3 ሰዎችን ወደ ስራ እየዱ እያሉ  ይዘው እጃቸውን ወደኃላ በማሰር በአንድ ትምህርት ቤት አካባቢ አለፍ ብለው ሁለቱ በጥይት ተመተው ሲሞቱ አንዱ  ሁለት ቦታ ተመጥቶ  ተርፈዋል፡፡  ሼኔ ትቀልባላቹ ታግዛላቹ በሚል የተያዙት፡፡ ከተያዙት መካከል ስማቸው ሁለቱ ጋርህ ባህሩ እና ማቲ ቡልቻ  ሲሆኑ ገበየው ተሸሜ የተባለው ደግሞ በሁለት ጥይት ተመተው በአሁኑ ጊዜ ለህኪምና እርዳታ ጤና ጣቢያ ይገኛል፡፡»
ምዕራብ ወለጋ፤ በፀጥታ ችግር የተዘጋዉ መንገድ ዳግም ሥራ ጀመረ

በወረዳው በዚህ ጥር ወር መጀመሪያ ላይ በአንድ ቦታ ከታጣቂዎች ጋር በተገናኙ የአምስት ሰዎች ህይወት ማለፉን ሌላው የአካባቢው ነዋሪ ተናግረዋል፡፡  በቅልቱ ካራ ወረዳ ተፈጸመዋል የተባለውን ሰላማዊ ሰዎች ጥቃት እና ህይወት ማለፈ ዙሪያ ማብራሪያ እንዲሰጡን የተጠየቅናቸው የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ተስፋ ፈይሳ ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርቷል፡፡ የትጥቅ እንቅስቃሴ በሚስተዋልበት በምዕራብ ወለጋ እና ሌሎችም የሀገሪቱ አካባቢዎች  ውስጥ የሰላማዊ ሰዎችም ግዲያና የንብረት ውድመት በተደጋጋሚ መከሰቱን በቅርቡ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ያወጣው ሪፖርትም ያመለክታል፡፡

ነጋሳ ደሳለኝ 
ኂሩት መለሰ
ፀሐይ ጫኔ
 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ
ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW