1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ሞሮኮ በ2,3 ቢሊዮን ዶላር ድሬዳዋ ውስጥ የማዳበሪያ ፋብሪካ ልትገነባ ነው

ቅዳሜ፣ ኅዳር 10 2009

ሞሮኮ የማዳበሪያ ማምረቻ ድሬዳዋ ከተማ ውስጥ በ2,3 ቢሊዮን ዶላር ለመገንባት ከኢትዮጵያ ጋር ስምምነት ተፈራረመች።

Marokko König Mohammed VI in Rabat
ምስል፦ Getty Images/C. Jackson

Morocco & Ethiopia agreements - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.

የዓለም ግዙፉ የፎስፌት ማዕድን ላኪ የሞሮኮ ኩባንያ (OCP) የማዳበሪያ ማምረቻ ኢትዮጵያ ውስጥ በ2,3 ቢሊዮን ዶላር ለመገንባት ከኢትዮጵያ ጋር ስምምነት ተፈራረመ። በኢትዮጵያ በኩል ስምምነቱን የፈረመው በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን መኾኑም ተገልጧል። የማዳበሪያ ማምረቻ ፋብሪካው የሚገነባው ድሬዳዋ ከተማ ውስጥ እንደሆነም ተዘግቧል። ሞሮኮ ዘርፈ-ብዙ በኾኑ የትብብር መስኮች የተለያዩ ውሎችን ከኢትዮጵያ ጋር መፈራረሟን የአዲስ አበባው ወኪላችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ የላከው ዘገባ ይጠቁማል። የሞሮኮ ንጉሥ 6ኛው በኢትዮጵያ ያደረጉትን የ2 ቀናት ጉብኝት አጠናቀዋል።

ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ

ማንተጋፍቶት ስለሺ

እሸቴ በቀለ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW