1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ራያ እና ሽረ በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት መያዛቸውን የክልሉ መንግሥት አረጋገጠ

ረቡዕ፣ ኅዳር 9 2013

የትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደብረፅዮን ገብረ ሚካኤል በሰጡት መግለጫ ራያ እና ሽረ በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት መያዛቸውን አረጋገጡ። ደብረጽዮን "ትግሉ አሁንም ቀጣይ ነው። ገና ነው። ውጊያ ውስጥ ነን" ብለዋል። ከትናንት በስቲያ የአውሮፕላን ጥቃት ያስተናገደችው መቐለ ትናንት እና ዛሬ መረጋጋት እንደታየባት ሚሊዮን ኃይለስላሴ ዘግቧል።

Äthiopien Debretsion G. Michael Präsident des Regionalstaates Tigray
ምስል DW/M. Hailesilassie

ራያ እና ሽረ በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት መያዛቸውን የክልሉ መንግሥት አረጋገጠ

This browser does not support the audio element.

የትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደብረፅዮን ገብረ ሚካኤል በሰጡት መግለጫ ራያ እና ሽረ በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት መያዛቸውን አረጋገጡ።

ደብረጽዮን "ትግሉ አሁንም ቀጣይ ነው። ገና ነው። ውጊያ ውስጥ ነን" ብለዋል። በትግራይ የተጀመረው ውጊያ አስራ ስድስት ቀናት ሆኖታል።

ከትናንት በስቲያ የአውሮፕላን ጥቃት ያስተናገደችው መቐለ ትናንት እና ዛሬ መረጋጋት እንደታየባት ሚሊዮን ኃይለስላሴ ዘግቧል። ሁሉም የግል እና የመንግሥት ባንኮች ተከፍተዋል። የነዳጅ እጥረት በመኖሩ የተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ መቀነስ መጀመሩን የገለጸው ሚሊዮን የስልክ እና የኢንተርኔት ግልጋሎቶች እንደተቋረጡ መሆናቸውን ዘግቧል።

ሚሊዮን ኃይለስላሴ

ኂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW