1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ በዓለም መሪዎች ሲታወሱ

ረቡዕ፣ ሚያዝያ 15 2017

ባለፈው ሰኞ የፋሲካ ማግስት የሮማው ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ በ88 አመታቸው ከዚህ አለም በሞት መለየታቸውን ተክትሎ የበርካታ አገሮችና የአለምቀፍ ድርጅቶች መሪዎች ሀዘናቸውን እየገለጹ ናቸው። የላቲን አሜሪካዋ አርጀንቲና ተወላጅ የሆኑት ፖፐ ፍራንሲስ ከደቡባዊው የዓለማችን ክፍል የወጡ የመጀመሪያው የአለም ካቶሊክ ቢተክርሲቲያን መሪ ነበሩ።

Italien | G7 Gipfel in Borgo Egnazia
ምስል Ciro Fusco/ZUMA Press/IMAGO

የአባ ፍራንሲስ ሕልፈት እና የመንግስታት መሪዎች አስተያየት

This browser does not support the audio element.

ፖፕ ፍራንሲስ በዓለም መሪዎች ሲታወሱ

ባለፈው ሰኞ የፋሲካ ማግስት የሮማው ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ በ88 አመታቸው ከዚህ አለም በሞት መለየታቸውን ተክትሎ የበርካታ አገሮችና የአለምቀፍ ድርጅቶች መሪዎች ሀዘናቸውን እየገለጹ ናቸው። የላቲን አሜሪካዋ አርጀንቲና ተወላጅ የሆኑት ፖፐ ፍራንሲስ ከደቡባዊው የዓለማችን ክፍል የወጡ የመጀመሪያው የአለም ካቶሊክ ቢተክርሲቲያን መሪ ነበሩ። ጳጳሱ በካቶሊክ ቢተክስርቲያን ለውጥ ያመጡ፣ ክድሆችና ከተገፉ ህዝቦች ጎን በመቆም የሚታውቁ፤ ለሰላም የሚሟገቱና የሚጮሁ እውነተኛ የድሆችና ጭቁኖች ጠበቃ ስለመሆናቸው ብዙ ተብሎላቸዋል፤ እየተባለላቸውም ነው ነው።

የመሪዎች የሀዘን መግለጫና መልዕክት

ዜና እረፍታቸው እንደተሰማም ብዙዎቹ የዓለም መሪዎች ስለጳጳሱ መልካም ተግባር በማውሳት በሞታቸው የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል።የአውሮፓ ህብረትና ኮሚሽን ፕሬዝዳንቶች በየግላቸው ቀድመው ባሰታላለፏቸው መልክቶች ፖፐ ፍራንሲስ አስተማሪነታቸውና አራያነታቸው ለካቶሊክ እመንት ተክታዮች ብቻ ሳሆን በሚሊዮን ለሚቆጠሩ የሌሎ እምነቶች ተከታዮችም  ጭምር ነበር በማለት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል። የጣሊያኗ ጠቅላይ ሚኒስተር ጆርጂያ  ሜሎኒ ደግሞ እሳቸው ትልቅ እረኛ ነበሩ በማለት በግላቸው አስተማሪያቸውና መካሪያቸው እንድነበሩ በሀዘን መግለጫቸው ገልጸዋል።

ፕሬዝዳንት ትሩምት ትናንት ከኋይት ሀውስ በሰጡት መግለጫም የፖፐ ፍራንሲሲን መልካም ሰውነትን አውስተው ለክብራቸው በመላ አሜሪክ ባንዲራ ዝቅ ብሎ እንዲውለበለብ ያዘዙ መሆኑን አስታውቀዋል፤ “ ለሳቸው ክብር የአሜሪካና የፌዴራል ግዝቶች ባንዲራዎች ጭምር ዝቅ ብለው እንዲውለበልቡ አዝዣለሁ” በማለት መልካም ሰውና አለምን የሚወዱ ታትሪ ሰው የነበሩ መሆኑን ገልጸዋል።

የሮማው ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ ሲታወሱ

የብራታኒያ ጠቅላይ ሚኒስተር ኪር ስታርመር ባወጡት መግለጫም ፖፕ ፍርናሲስን “የድሆችና የተገፉ ህዝቦች ጳጳስ ነበሩ” በማለት የተሻለ አለም እኒዲፈጠር የሚጥሩና ተስፋም የሚያደርጉ ነበሩ ሲሉ ገልጸዋቸዋል።

ዜና እረፍታቸው እንደተሰማም ብዙዎቹ የዓለም መሪዎች ስለጳጳሱ መልካም ተግባር በማውሳት በሞታቸው የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል።ምስል Andrew Medichini/AP Photo/picture alliance

ዋና ጸሀፊ ጉቴረሽና ሌሎች ስለ ፓፓው

የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንንቶኒዮ ጉቴረሽም የፖፕ ፍርንሲስ ሞት ሀዘን ለካቶሊኮች ብቻ ሳይሆን በምግባራቸውና በትምህርታቸው በአራያነት ለሚከተሏቸው ሁሉ መሆኑን በመግለጽ  ትተውት ያለፉትን ውርስ አውስተዋል፤ “ የእምነትን የአግልግሎትን፤ ለሁሉም በተለይም ለተገለሉና በጦርነት ውስጥ ለሚሰቃዩ ፍቅርንና አጋርነትን የማሳየትን አስፈላጊነት ትተው አልፈዋል” ብለዋል።

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ባስተላለፉት መልክትም  ፖፐ ፍራንሲስ ለካቶሊሊክ ቤተክርስቲያን ምእመናን ብቻ ሳይሆን ለዓለም  ባጠቃላይ ትልቅ ስራ የሰሩ  መሆኑን በመግለጽ ህዘናቸውን ለመላ ክርስቲያኖች በተለይም ለካቶሊኮች አስተላልፈዋል።

በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቼስኮስ ህልፈት የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን አስተያየት

የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ፤ ፖፕ ፍራንሲስን “ሁላችንንም ጥሩ ላማድረግ የሞከሩ የተለዩ መሪ ነበሩ” ሲሉ ገልጸዋቸዋል ባወጡት መግለጫ።

የጀርመኑ ቻንስለር ሹልዝ በኤክስ ገጻቸው በፖፐ ፍራንሲስ ሞት  የካቶሊክ ቤተክርስቲያንና አለም በሙሉ የድሆች ጠበቃ፤ የሰላም ተሟጋችና ሰላም ሰባኪን አተዋል ሲሉ አስፍረዋል ።

የቱርክ፣ የእስራኤልና ፍልስጤም መሪዎችም የጳጳሱን መልካም ሰውነት በማውሳት ሀዘናቸውን ከገለጹት ያለም መሪዎች ውስጥ ናቸው። የበርካታ የእስያ፤ የላቲን አሜሪካና የአፍሪካ  አገሮች መሪዎችም በጳጳሱ ሞት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል፤በመግለጽም ላይ ናቸው።

የፋራንሲስ የኮንጎ እና የደቡብ ሱዳን ጉብኝት

የቀብር ስነስራት

ፖፐ ፍርንሲስ 1.4 ቢሊዮ አማኞች እንዳላት ለሚነገርላት የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ የሆኑት እ እ እ 2013 ነው። የቀብራቸው ስንስራት ከሰላሳ በላይ የአገር መሪዎችና  በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ምዕመናን በተገኙበት በሮም የሴንት ፒተር አደባባይ በሚቀጥሚለው ቅዳሜ የሚፈጸም መሆኑ ታውቋል።

ገበያው ንጉሴ

ታምራት ዲንሳ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW