ሰባት ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሊዋሃዱ ነው
ሐሙስ፣ ኅዳር 20 2011ማስታወቂያ
ሰባት የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለመዋሃድ ተስማሙ። ከሰባቱ አምስቱ ከሀገር ውጭ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ናቸው። በሀገር ውስጥ ሲሰሩ የቆዩቱ ሁለት ፓርቲዎች የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ እና የኦሞ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ህብረት ሲሆኑ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ የሽግግር ምክር ቤት፣ የኢትዮጵያ መድህን ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ ብሩህ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ እና ኢትዮጵያችን ህዝባዊ ንቅናቄ ደግሞ መቀመጫቸውን ከሀገር ውጭ ያደረጉ ናቸው።
ሰባቱ ፓርቲዎቹ የአቋም መግባባት ላይ ለመድረስ ለበርካታ ወራት ሲደራደሩ መቆየታቸውን ለDW ተናግረዋል። የአዲስ አበባው ወኪላችን ዩሃንስ ገብረእግዚያብሔር ያጠናቀረውን ሙሉ ዘገባ ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ።
ዩሃንስ ገብረእግዚያብሔር
ተስፋለም ወልደየስ
ኂሩት መለሰ