1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ሱዳን ድንበሮቿን መዝጋቷ

ቅዳሜ፣ ጥቅምት 28 2013

ሱዳን ከወቅቱ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ሁኔታ ጋር በተገናኘ የሚያጎራብታትን የድንበር አካባቢ መዝጋቷን የሀገሪቱ የዜና ምንጮች ይፋ አድርገዋል። የመተማ ዮሐንስ ከተማ ነዋሪ ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት ኬላው ቀደም ሲል በኮቪድ ምክንያት ተዘግቶ የቆየ ቢሆንም ለጥቂት ቀናት ከተከፈተ በኋላ ሰሞኑን ከተፈጠረው አገራዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ እንደገና ተዘግቷል፡፡

Grenzenkontrolle am Metema zwischen Äthiopian und Sudan
ምስል፦ DW/A. Mekonnen

«ከወቅታዊ አገራዊ ሁኔታው ጋር በተገናኘ መዘጋቱ»

This browser does not support the audio element.

ኢትዮጵያውያንና ሱዳናውያንን ከሚያገናኙ ኬላዎች መካከል አንዱ የመተማ ገላባት ኬላ ነው፡፡ መተማና ገላባት ከተሞች የሚለያዩት 30 ሜትር በሚረዝም አንድ ድልድይ ነው፤ አንዱ ወደሌለኛው በመሻገር ከፍተኛ የንግድ ልውውጥ ያደርጋሉ፣ ሱዳንንና ኢትዮጵያን በየብስ የሚያገናኘው አቢይ መንገድም በዚሁ አቅጣጫ ይገኛል፡፡ ኬላው በተለያዩ ምክንያቶች አንዴ ይዘጋል፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ ይከፈታል፣ በቅርቡ ከኮቪድ ጋር በተገናኜ በፌደራል መንግስት ኬላው ተዘግቶ አንደነበር ነዋሪዎች ይናገራሉ፣ ለጥቂት ቀናት አገልግሎት መስጠት ቢጀምርም ሰሞኑን ደግሞ ከኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ አገልግሎቱን አቋርጧ፡፡ አንድ የመተማ ዮሐንስ ከተማ ነዋሪ ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት ኬላው ቀደም ሲል በኮቪድ ምክንያት ተዘግቶ የቆየ ቢሆንም ለትቂት ቀናት ከተከፈተ በኋላ ሰሞኑን ከተፈጠረው አገራዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ እንደገና ተዘግቷል፡፡ ሱዳን ከወቅቱ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ሁኔታ ጋር በተገናኘ የሚያጎራብታትን የድንበር አካባቢ መዝጋቷን የሀገሪቱ የዜና ምንጮች ይፋ አድርገዋል። ከባሕር ዳር ዘጋቢያችን ዓለምነው መኮንን ዘገባ አለው።
ዓለምነው መኮንን

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW