1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ
ውዝግቦችአፍሪቃ

ሳልሳይ ወያነ ትግራይ የህወሓት ወታደራዊ ክንፍን መክሰሱ

ማክሰኞ፣ መጋቢት 9 2017

በተቃዋሚነት የሚንቀሳቀሰው ሳልሳይ ወያነ ትግራይ የህወሓት ወታደራዊ ክንፍ በሰላማዊ ዜጎች ላይ ግድያን ጨምሮ የተለያዩ የመብት ጥሰቶች እየፈፀመ ነው አለ። ፓርቲው ሰሞኑን በዓዲጉደምና ሞኾኒ ከተፈጠሩ ሞትን ያስከተሉ ክስተቶች ተጨማሪ በሌሎች ተጋሩ ላይም በደሎች እየተፈፀሙ ነው፥ ለዚህም ተጠያቂዎቹ የህወሓት ፖለቲካዊና ወታደራዊ ክንፎች ናቸው ብሏል።

Äthiopien | Ato Alul Haidu und Ato Birhane Atsibeh - Salsai Wayane Tigray Vorsitzender und Leiter
ምስል፦ Million Hailesilassie/DW

ሳልሳይ ወያነ ትግራይ የህወሓት ወታደራዊ ክንፍን መክሰሱ

This browser does not support the audio element.

በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ያወጣው በትግራይ በተቃዋሚነት የሚንቀሳቀሰው ሳልሳይ ወያነ ትግራይ፥ ከጦርነቱ ከፍተኛ ጉዳት ባላገገመችው ትግራይ ለአንድ የፖለቲካ ሐይል ባጋደሉ ታጣቂዎች ከባድ የሰብአዊ መብት ጥሰት እየፈፀሙ ነው ብሏል። ሰሞኑን በዓዲጉደም እና ሞኾኒ ከተፈጠሩ ሞትን ያስከተሉ ክስተቶች በተጨማሪ በሌሎች ተጋሩ ላይም የተለዩ በደሎች እየተፈፀሙ ነው ሲል ገልጿል። የእነዚህ ጥፋቶች ተጠያቂ «የህወሓት ፖለቲካዊ ክንፍ» መሆኑ ደግሞ ለእነዚህ ተግባራት «የሕግ ማስከበር እርምጃ» በማለት ሓላፊነት ወስዷል ያለው ተቃዋሚው ፓርቲው፥ የህወሓት ወታደራዊ ክንፍን ትዕዛዝ ተቀብለው በንጹሐን ላይ እጃቸውን የሚያነሱት ደግሞ ከተጠያቂነት አያመልጡም ብሏል።

ለዶቼቬለ የተናገሩት የሳልሳይ ወያነ ትግራይ ሊቀመንበር አሉላ ሃይሉ፥ የህወሓት ወታደራዊ ክንፍ የአስተዳደር አካላትን «ለነሱ ታማኝ በሆኑ የመቀየር» ሕገወጥ ተግባር እየፈፀሙ ነው፥ ይህ ደግሞ በትግራይ ከፍተኛ አደጋ ፈጥሮ ይገኛል ብለዋል። ከዚህ በተጨማሪም ሳልሳይ ወያነ ትግራይ በክልሉ ያለውን ፖለቲካዊ ቀውስ ለመፍታት ሁሉም ሐይሎች የሚያሳትፍ «ብሔራዊ ጉባኤ» ተጠርቶ መፍትሔዎች ማበጀት ይገባል ይላል።

ከዚህ በተጨማሪ ተቃዋሚው ፓርቲ ሳልሳይ ወያነ ትግራይ በትናንቱ መግለጫው ጨምሮ እንዳለው፥ እያንዳንዱ የትግራይ ሠራዊት አባል ራሳቸውን «ኮር እና ከኮር በላይ» ብለው ከሚጠሩ የህወሓት ወታደራዊ ክንፍ አዛዦች የሚሰጥ ንጹሐን ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እንዳይቀበሉ ጥሪ አቅርቧል።

በትግራይ በተለይም ባለፈው ሳምንት የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር መፈንቅለ መንግሥት ያለው እና በታጣቂዎች የተደገፈ የአስተዳደር አካላትን የመቀየር ተግባራት በተለያዩ ከተሞች እና ወረዳዎች የታየ ሲሆን፥ ይህን ተግባር በዶክተር ደብረፅዮን የሚመራው የህወሓት ክንፍ "«ሕግ ማስከበር» እንቅስቃሴ እንዳለው ይታወሳል።

ሚሊየን ኃይለ ሥላሴ

ሸዋዬ ለገሠ

አዜብ ታደሰ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW