1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት

ረቡዕ፣ ሰኔ 20 2010

ሁለቱ ወገኖች ተኩስ አቁም ተግባራዊ በሚሆንበት መንገድ እና  ስለ ሥልጣን ክፍፍል እዚያው ካርቱም ውስጥ መወያየት እንደሚቀጥሉ የሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አል ዲርዲሪ ሞሀመድ አህመድን ጠቅሶ ዘግቧል። የአማጽያኑ መሪ ማቻር ለሥልጣን ክፍፍል እንዲያመች ለደቡብ ሱዳን ሦስት ዋና ከተማ እንዲኖር የቀረበውን ሃሳብ መቃወማቸው ተዘግቧል።

Südsudan  Friedenstreffen - Präsidenten Salva Kiir und Rebellenführer Machar
ምስል Reuters/M. Nureldin Abdallah

ኪር እና ማቻር የሰላም ስምምነት ተፈራረሙ

This browser does not support the audio element.

የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳላቫ ኪር እና የአማጽያኑ መሪ ሪየክ ማቻር ዛሬ ካርቱም ውስጥ የሰላም ስምምነት ተፈራረሙ። ሁለት ወገኖች ካርቱም ሱዳን ውስጥ ለሁለት ቀናት ካካሄዱት ድርድር በኋላ የተፈራረሙት ስምምነት ተኩስ አቁምን ያካትታል። የሰላም ስምምነቱ ዓላማም በአስር ሺህዎች የሚቆጠር ህዝብ ህይወት የጠፋበትን ጦርነት ማስቆም መሆኑ ተገልጿል።  ሁለቱ ወገኖች ተኩስ አቁም ተግባራዊ በሚሆንበት መንገድ እና ስለ ሥልጣን ክፍፍል እዚያው ካርቱም ውስጥ መወያየት እንደሚቀጥሉ የሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አል ዲርዲሪ ሞሀመድ አህመድን ጠቅሶ ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል። የአማጽያኑ መሪ ማቻር ለሥልጣን ክፍፍል እንዲያመች ለደቡብ ሱዳን ሦስት ዋና ከተማ እንዲኖር የቀረበውን ሃሳብ መቃወማቸው ተዘግቧል። 


ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ 
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW