የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለጫ
ሐሙስ፣ መጋቢት 20 2010ማስታወቂያ
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ይህን በመጥቀስ በአካባቢውም ሆነ በርቀት የሚገኙ እና ሀገሪቱ የነበረችበት አስቸጋሪ ሁኔታ ይከታተሉ የነበሩ ሃገራት መንግሥታት መሪዎች እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ገዢዉ ፓርቲ የሊቀመንበር ምርጫዉን በሰላም በማጠናቀቁ የደስታ መልዕክት እየላኩ መሆኑን ዘርዝረዋል። ሳምንታዊ በሆነዉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ለሕዳሳዉ ግድብ በሚደረገው የቦንድ ሽያጭ መካከለኛዉ ምሥራቅ ከሚገኙ ዜጎች ከፍተኛው ገቢ መገኘቱም ተነግሯል። መግለጫውን የተከታተለው ዘጋቢያችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ከአዲስ አበባ ዝርዝሩን ልኮልናል።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ሸዋዬ ለገሠ
ነጋሽ መሐመድ