ስለሳይንስና ሥነ-ቴክኒክ ፣ ምክር ከታዋቂ መምህር፤
ረቡዕ፣ ጥር 9 2004ማስታወቂያ
የተለያዩ ማዕድናትና ጥሬ ሀብቶች ባሏቸው አገሮች ዕውቀት ሲስፋፋ ፤ ዕድገቱ እጅግ ሊፋጠን ይችላል። አንዳንድ አገሮች ደግሞ አሉ፣ ፤ እንደ ጃፓንና ጀርመን የመሳሰሉ። ትልቁ ሀብታቸው ፣ ትምህርት ፣ ምርምር ፣ በተለይም ከፍተኛ የሳይንስ ምርምር ነው። የኢንዱስትሪ ምርቶቻቸው የዓለምን ገበያ፣ የሚያጥለቀልቀውም ፣ ኩባንያዎቻቸውና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ፤ ለአዳዲስ የፈጠራ ሥራዎች የሚፈለጉ ወጣቶችን በማስተማር ጠንካራ ድጋፍ ስለሚሰጡ ነው። ይህን ከሞላ -ጎደል ኀያላኑ መንግሥታት ሁሉ ይፈጽሙታል። አንድ ጥሩ ምሳሌ፤ ባለፈው ኅዳር ፤ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ፤ በሳይንስ ፣ ሂሳብና ኢንጂኔሪንግ በማስተማር ለታወቁ ለ 9 ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ፕሮፌሰሮችና ሌሎችም ባለሙያዎች ሽልማት መስጠታቸው ነው። ሽልማቱን ከተቀበሉት መካከል፤ሳይንስ በተለይም ፊዚክስ ኢትዮጵያን ለመሰለ አዳጊ ሀገር ሊሰጥ ስለሚችለው ጠቀሜታ ያነጋገርናቸው የዛሬው የሳይንስና ኅብረተሰብ ዝግጅት እንግዳችን ፣ ዩናይትድ እስቴትስ ውስጥ ፣ በሰሜን ካሮላይና ፌደራል ክፍለ ሀገር የግብርናና ቴክኒክ ዩኒቨርስቲ ፕሮፌሰር ሰሎሞን ቢልልኝ ናቸው።
ተክሌ የኋላ
አርያም ተክሌ