ስለ ካቢኔ አባላት አስተያየት ከአማራ ክልል
ረቡዕ፣ መስከረም 26 2014ማስታወቂያ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ዛሬ የተፎካካሪ የፖለቲካ ድርጅት አባላትን ያካተተ ካቢኔያቸውን አቋቁመዋል። የዘንድሮው የካቢኔ አባላት ሰብጥር ሌሎች የፖለቲካ ድርጅት አባላትን ማካተቱ መልካም ጅምር መሆኑን በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢ ነዋሪዎች አስተያየቶችን ሰጥተዋል። አንዳንዶቹ በምደባው ብዙ አዳዲስ ፊቶችን አላየንምሲሉ ሌሎች ደግሞ የሴቶች ተዋፅኦ ከክልሎች የተሸለ ቢሆንም አሁንም ይቀራል ባዮች ናቸው፣ አንዳንድ ምደባዎች ደግሞ የትምህርት ዳራን ያላማዕከሉ ናቸው ሲሉ ተችተዋል። በተለይ ትምህርትና ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሮች ከሙያቸው ጋር የተቀራረበ ምደባ ሊደረግላቸው ይገባ እንደነበር ተናግረዋል። አስተያቶቹን የባህር ዳሩ ወኪላችን ዓለምነው መኮንን አሰባስቧቸዋል።
ዓለምነው መኮንን
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ሸዋዬ ለገሰ