ሳይንስ
«ስማርት» መታወቂያ
ረቡዕ፣ ጥቅምት 26 2012ማስታወቂያ
የመቀሌ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የመታወቂያ ደብተርን የሚተካ ሶፍትዌር በቅርቡ አዘጋጀተዋል።«ስማርት አይዲ» የተባለዉ ማንነትን መለያ መተግበርያ ወይም application የዜጎችን ዝርዝር መረጃዎች የሚይዝ፣ የወረቀት አሰራርን የሚያስቀር እና ሕገ ወጥ መረጃን ለመለየት የሚያስችል ነው፡፡አበልፃጊዎቹ የመቀሌ ቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት የ2011 ዓ.ም የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ምሩቃን የሆኑት ኪዳነ ገብረመድህን፣ አረጋዊ ሀይለየሱስና ሌሎች ባልደረቦቻቸው ሲሆኑ ከመታወቂያ አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የሚገጥሙ ችግሮችን ለመፍታት አልመው እንደሰሩት ተናግረዋል፡፡ሶፍትዌሩ በሀገር ውስጥ ቋንቋዎች የሚሰራ መሆኑም አበልፃጊዎቹ ይናገራሉ።የመቀሌዉ ወኪላችን ሚሊዮን ኃይለስላሴ በዛሬዉ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዝግጅታችን አዲሱን ቴክኖሎጂና አበልፃጊዎቹን ያስተዋዉቀናል።
ሚሊዮን ኃይለስላሴ
ነጋሽ መሐመድ