ስደተኝነት በስደተኛዉ ብዕር
ሐሙስ፣ ነሐሴ 15 2006ማስታወቂያ
ወደ ቤቴ የምትወስድኝን ከለሌቱ ስድስት ሰዓት ከሩብ ላይ ያለችዉን የመጨረሻዋን ባቡር እይዛለሁ። የምኖርበት ቦታ ሩቅ ስለነበር ወደ ቤቴ በምሄድበት ሰዓት አዉቶቡስ አይኖርም። በመሆኑም ሌሊት ሰባት ሰዓት ላይ ከባቡር ወርጄ ከሃያ ደቂቃ በላይ የእግር መንገድ ይጠብቀኛል። በተለይ ክረምት ሲሆን ከቅዝቃዜዉ ጋር ዝናብ ወይም በረዶ እየደበደበኝ እቤቴ ስገባ ከለሊቱ ሰባት ሰዓት ተኩል ይሆናል።»
ሲሉ የግል የስደት ተሞክሮአቸዉን 174 ገጽ ባለቻት አነስተኛ መፅሐፍ አቅርበዋል። በጀርመን የስደቱ ዓለምን ከተቀላቀሉ 12 ዓመታትን አስቆጥረዋል። አቶ አስፋዉ በመጽሐፋቸዉ፤ በጀርመን በቆዩበት ዓመታት በማህበረሰቡ ያጋጣማቸዉን የተለያዩ ገንቢ ጉዳዮች እና ባህል ለአንባብያን ለማቅረብ፤ በተለይ ሥለ ጀርመናዉያን ያወቁትን ለማሳወቅ እንደሞከሩ ይናገራሉ። በዕለቱ ዝግጅታችን ፀሀፊ አስፋዉ ከበደን እና ሌላ በጀርመን በስደት ላይ ያሉ ኢትዮጵያዊን የግል አስተያየታቸዉን አንዲያካፍሉን ጋብዘናል። ሙሉ ቅንብሩን የድምፅ ማዕቀፉን በመጫን ይከታተሉ።
አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሃመድ