1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ስደተኞችን በመግደል የተጠረጠሩ መያዛቸዉ

ሐሙስ፣ ሐምሌ 17 2006

በደቡባዊ ጣሊያን በሲሲሊ ግዛት የካታኒያ ከተማ ፖሊስ ከሊቢያ ወደጣሊያን ያቀኑ የነበሩ ስደኞችን የጫነች ጀልባ ዉስጥ ስደተኞችን ገድለዉ ባህር ዉስጥ በመወርወር የተጠረጠሩ አምስት ሰዎች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታዉቋል።

Italien Flüchtlingsdrama Lampedusa Flüchtlingsboot
ምስል፦ picture-alliance/ROPI

በጩቤ ተወግተዉና ተደብድበዉ ወደባህር የተወረወሩት ቁጥር ወደስልድሳ እንደሚጠጋ ጀልባዉ ዉስጥ የነበሩ የዓይን እማኞችን ዋቢ በማድረግ የገለፀዉ የካታኒያ ፖሊስ በደቡባዊ ላምፔዱዛ ከጀልባዉ ሞተር ከሚወጣዉ መርዛማ ጭስ የተነሳ መተንፈስ ሳይችሉ ቀርተዉ በመታፈን 29ሰዎችም መሞታቸዉንም አመልክቷል። ከስደተኞቹ የአንዱ ሕይወትም በካርቦን ሞኖክሳይድ ታፍኖ ወደሃኪም ቤት ሲወሰድ ማለፉም ተገልጿል።

ተኽለእዝጊ ገ/ኢየሱስ

ሸዋዬ ለገሠ

ኂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW