ስደተኞችን የማንሳት ዘመቻ በፓሪስ
ሐሙስ፣ ግንቦት 23 2010![Frankreich Polizei räumt Migranten-Zeltlager in Paris](https://static.dw.com/image/43988799_800.webp)
ማስታወቂያ
በፓሪስ ጎዳናዎች እና በወንዞች ዳርቻ ሰፍረው ከሚገኙት ቁጥራቸው ወደ 3 ሺህ ይጠጋል ከተባሉ ስደተኞች መካከል ትናንት 1 ሺህ ያህሉን ፖሊስ አስነስቷል። እነዚሁ ስደተኞች በጊዜያዊነት በተዘጋጀላቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ጅምናዚየሞች ነው የተወሰዱት። ከመካከላቸው አብዛኛዎቹ የሱዳን የኤርትራ እና የኢትዮጵያ እንዲሁም የአፍጋኒስታን ስደተኞች መሆናቸው ተነግሯል። ተገን ጠያቂ ስደተኞቹ በትናንሽ ድንኳኖች ተጠልለው ይኖሩባቸው ከነበሩት ከነዚህ ስፍራዎች በመነሳታቸው ተደስተዋል። የፓሪስ ከተማ ባለሥልጣናትም ስደተኞቹን ማንሳቱ በመሳካቱ ረክተናል ብለዋል። ዝርዝሩን የፓሪስዋ ዘጋቢያችን ሃይማኖት ጥሩነህ አዘጋጅታዋለች።
ሃይማኖት ጥሩነህ
ኂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ