1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ስደተኞችን የማንሳት ዘመቻ በፓሪስ

ሐሙስ፣ ግንቦት 23 2010

አብዛኛዎቹ የሱዳን የኤርትራ እና የኢትዮጵያ እንዲሁም የአፍጋኒስታን ስደተኞች መሆናቸው ተነግሯል። ተገን ጠያቂ ስደተኞቹ በትናንሽ ድንኳኖች ተጠልለው ይኖሩባቸው ከነበሩት ከነዚህ ስፍራዎች በመነሳታቸው ተደስተዋል።

Frankreich Polizei räumt Migranten-Zeltlager in Paris
ምስል፦ Getty Images/AFP/G. Julien

ስደተኞችን የማንሳት ዘመቻ በፓሪስ

This browser does not support the audio element.


በፓሪስ ጎዳናዎች እና በወንዞች ዳርቻ ሰፍረው ከሚገኙት ቁጥራቸው ወደ  3 ሺህ ይጠጋል ከተባሉ ስደተኞች መካከል ትናንት 1 ሺህ ያህሉን ፖሊስ አስነስቷል። እነዚሁ ስደተኞች በጊዜያዊነት በተዘጋጀላቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ጅምናዚየሞች ነው የተወሰዱት። ከመካከላቸው አብዛኛዎቹ የሱዳን የኤርትራ እና የኢትዮጵያ እንዲሁም የአፍጋኒስታን ስደተኞች መሆናቸው ተነግሯል። ተገን ጠያቂ ስደተኞቹ በትናንሽ ድንኳኖች ተጠልለው ይኖሩባቸው ከነበሩት ከነዚህ ስፍራዎች በመነሳታቸው ተደስተዋል። የፓሪስ ከተማ ባለሥልጣናትም ስደተኞቹን ማንሳቱ በመሳካቱ ረክተናል ብለዋል። ዝርዝሩን የፓሪስዋ ዘጋቢያችን ሃይማኖት ጥሩነህ አዘጋጅታዋለች።
ሃይማኖት ጥሩነህ 
ኂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW