1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ስጋት ያስከተለው የአዋሽ ወንዝ ሙላት

ዓርብ፣ ነሐሴ 29 2012

ገደቡን አልፎ አካባቢውን ያጥለቀለቀው የአዋሽ ወንዝ በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን በሚገኝ ትምህርት ቤት ላይ የከፋ ጉዳት ማድረሱ ተሰማ። የትምህርት ቤቱ ዕርሰ መምህርት እንደተናገሩት ወንዙ እንዲህ ሲሞላ ፍፁም ታይቶ አይታወቅም። ከትምህርት ቤቱ ውጭም በአርሶ አደሮች ማሳ ላይ ያደረሰ ሲሆን በውኃ የተከበበው ይህ ስፍራ እንደ ደሴት ሆኗልም ነው ያሉት።

Äthiopien | Überschwemmungen des Fluss Awash
ምስል፦ DW/S. Getu

«ከዚህ በፊት እንዲህ ሞልቶ ታይቶ አይታወቅም»

This browser does not support the audio element.

ከአፍ አስከ ገደፉ እየተጥለቀለቀ ያለው የአዋሽ ወንዝ በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን መርቲ-የጁ ወረዳ በትምህርት ቤት ላይ የከፋ ጉዳት ማድረሱን የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህርት ለዶይቼ ቨሌ ተናገሩ። የወንዙ በዚህ ደረጃ መሙላት ፍጹም ታይቶ የማይታወቅ ነው ያሉት ወ/ሮ ሰዓዳ ከድር ከትምህርት ቤቱም ውጭ የአርሶ አደሮች ማሳ ላይ ውሃው ጉዳት ማድረሱን አድርሷል፤ አከባቢው በውሃ ሙላት ተከቦም ደሴት ሆኗልም ነው ያሉት። አሁን ከመርቲ የጁ ወደ የትኛውም ስፍራ የሚወስዱ መንገዶች በውኃ መሸፈኑን፤ በዚህ የሚቀጥል ከሆነም ጎርፍ ወደ ሰዎች መኖሪያ መግባቱ አይቀሬ ነውም ይላሉ። በአከባቢው የሚገኘው የላይኛው አዋሽ ተፋሰስ አግሮ ኢንደስትሪ በበኩሉ እስካሁን በካምፕና በነዋሪዎች ላይ የጎርፍ አደጋው እንዳይከሰት ጥረት ቢደረግም ከ70 ሄክታር በላይ የጥጥ አንዲሁም 30 ሄክታር የሚገመት የብርቱካን እርሻ በውኃ መዋጡን አስታውቋል። የኢንደስትሪው የውኃ ክፍል ኃላፊ አቶ መንክር ግርማ ከዚህ በፊት በታሪክ ጎርፍ ደርሶበት የማያውቀው ስፍራ ሁሉ በውኃ እየተሸፈነ መሆኑን ገልጸዋል። ከቆቃ ግድብ የሚለቀቅ ውኃ ለአከባቢው በጎርፍ መጥለቅለቅ ጉልህ ድርሻ ቢኖረውም የአከባቢው ገባር ወንዞች በውል አለመጠናታቸው ደራሽ ውሃውን የማይገመት ማድረጉንም ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ ዝርዝሩን የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ስዩም ጌቱ ልኮልናል።

ምስል፦ DW/S. Getu

ዓለምነው መኮንን

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW