1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ስፓኝና የህብረቱ የፕሬዝዳንትነት ስልጣን

ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 29 2002

ከጎርጎሮሳውያኑ 2010 ዓ.ም መጀመሪያ አንስቶ የአውሮፓ ህብረት የ52 ዓመታት ታሪክ ተቀይሯል ።

የስፔይን የአውሮፓ ህብረት የፕሬዝዳንትነት አርማ

በየስድስት ወሩ በዙር የሚደርሰውን ህብረቱን የመምራት ሀላፊነት የሚረከቡት አባል ሀገራት እንደ ከዚህ ቀደሙ ሙሉ የፕሬዝዳንትነት ስልጣን አይኖራቸውም ።አሁን ስራቸውን የሚያግዝ ቋሚ ባለስልጣን አግኝተዋል የሊዝበኑ ውል መተግበር ከጀመረ ከአንድ ወር በኃላ ስፓኝ የተረከበችው የአሁኑ የስድስት ወራት የመሪነት ስልጣንዋ ከቀድሞዎቹ ይለያል ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ሆሴ ማኑዌል ሮድሪጌዝ ዛፓቴሮምስል AP

ሁለቱ አዳዲስ የአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ ባለሥልጣናት በሊዝበኑ ውል መሰረት በአውሮፓ ህብረት ፅህፈት ቤት ብራሰልስ የሚካሄዱ ዐብይ ጉባኤዎችን ሲመሩ የስፓኝ ሚና ከሁለቱ ባለሥልጣናት ያነሰ ነው የሚሆነው ። አንዱ ተግባሯ የህብረቱን ከፍተኛ ሀላፊዎች ማገዝ ነው ። በሚኒስትሮች ደረጃ የሚካሄዱ ዋና ዋና ስብሰባዎችንና ከህብረቱ ውጭ ከሆኑ አገራት ጋር የሚካሄዱ ጉባኤዎችንም ማስተናገድ ይጠበቅባታል ።

ሂሩት መለሰ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW