ስፓኝና የህብረቱ የፕሬዝዳንትነት ስልጣን
ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 29 2002ማስታወቂያ
በየስድስት ወሩ በዙር የሚደርሰውን ህብረቱን የመምራት ሀላፊነት የሚረከቡት አባል ሀገራት እንደ ከዚህ ቀደሙ ሙሉ የፕሬዝዳንትነት ስልጣን አይኖራቸውም ።አሁን ስራቸውን የሚያግዝ ቋሚ ባለስልጣን አግኝተዋል የሊዝበኑ ውል መተግበር ከጀመረ ከአንድ ወር በኃላ ስፓኝ የተረከበችው የአሁኑ የስድስት ወራት የመሪነት ስልጣንዋ ከቀድሞዎቹ ይለያል ።
ሁለቱ አዳዲስ የአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ ባለሥልጣናት በሊዝበኑ ውል መሰረት በአውሮፓ ህብረት ፅህፈት ቤት ብራሰልስ የሚካሄዱ ዐብይ ጉባኤዎችን ሲመሩ የስፓኝ ሚና ከሁለቱ ባለሥልጣናት ያነሰ ነው የሚሆነው ። አንዱ ተግባሯ የህብረቱን ከፍተኛ ሀላፊዎች ማገዝ ነው ። በሚኒስትሮች ደረጃ የሚካሄዱ ዋና ዋና ስብሰባዎችንና ከህብረቱ ውጭ ከሆኑ አገራት ጋር የሚካሄዱ ጉባኤዎችንም ማስተናገድ ይጠበቅባታል ።
ሂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ