ሶማሊያና ተመድ
ዓርብ፣ ሚያዝያ 13 2009![Somalia Mogadischu - U.N. Generalsekretär Antonio Guterres bei Pressekonferenz](https://static.dw.com/image/37839111_800.webp)
ማስታወቂያ
የሶማሊያ መንግሥት የሐገሪቱን ፀጥታ ለማስከበር እና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ተባብሮ እየሠራ መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታወቀ።ድርጅቱ እንደሚለዉ ሶማሊያ ከዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ እና ከአካባቢዉ ማሕበራት ጋር የመሠረችዉ ትብብር የፀጥታ ኃይሏን ለማጠናከር፤ ረሐብን ለመከላከል፤ ሙስናን ለመዋጋት እና የመንግሥቱን መዋቅር ለማጎልበት ጠቃሚ ነዉ።የሶማሊያን ጉዳይ የሚከታተሉ አንድ የማሕበራዊ ጉዳይ ምሑር ግን የዓለም አቀፉን ድርጅት ተስፋ ብዙም አልተቀበሉትም።የዋሽንግተን ዲሲዉ ወኪላችን መክብብ ሸዋ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።
መክብብ ሸዋ
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ