1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጦር መውጣት በኋላ

ሰኞ፣ ጥር 18 2001

የመጨረሻዎቹ የኢትዮጵያ ወታደሮች ዛሬ ጠዋት ወጥተዋል። ከሶማሊያ ሙሉ በሙሉ ወጥተዋል። በባይዶዋ ብቻ ነበር የቀሩት፤ እነሱም ትናንት ማታ ለቀዋል። አሁን ባዶ በቀሩት ወታደራዊ ይዞታዎች ግጭት ተፈጥሮ ፖሊስና ታጣቂ ሚሊሺያን ጨምሮ ሁለት ሰዎች ተገድለዋል።

ሶማሊያ
ሶማሊያ
የኢትዮጵያ ጦር ዛሬ ጠዋት ሶማሊያን ሙሉ በሙሉ ለቆ መውጣቱ ተገለፀ። በተፈጠረው የሀይል ክፍተት የሶማሊያ የሽግግር መንግስት ስጋት ውስጥ ወድቓልም ተብሏል። በዚህ ሳምንት ጅቡቲ ውስጥ ሊደረግ በታቀደው ሁሉን አቀፍ የሶማሊያውያን ጉባኤ ላይ የሚሳተፉ የሶማሊያ ህግ አውጪ አካላት ደግሞ አዲስ ፕሬዚዳንት ለመምረጥ ተጨማሪ ጊዜ እንደሚያስፈልጋቸው ገልፀዋል።
ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW