ሶርያና የአውሮጳ ህብረት ማዕቀብ
ረቡዕ፣ የካቲት 21 2004ማስታወቂያ
የአውሮጳ ህብረት አባል ሀገሮች የውጭ ጉዳይ ሚንስትሮች ትናንት ባካሄዱት ስብሰባቸው በሶርያ መንግሥት ላይ ተጨማሪ የኤኮኖሚ ማዕቀብ፡ በሶርያ ባለሥልጣናትም ላይህብረቱ ካሁን ቀደም በአንድ መቶ ሠላሣ ስምንት ሰዎችና ድርጅቶች ንብረት እንዳይንቀሳቀስ የጣለው ማዕቀብ እንደጸና የሚቆይ ሲሆን፡ አዲሱ ማዕቀብከሶርያ ጋ በወርቅና በከበሩ ደንጊያዎች ንግድ እንዳይካሄድ ፡ የዕቃ ማጓጓዣ አውሮፕላኖች ወደ ህብረቱ ሀገሮች እንዳይገቡ ወይንም ከህብረቱ ሀገሮች ተመሳሳይ ጉዞ ወደ ሶርያ እንዳይደረግ ያዛል።
በሌላ በኩል በሶርያ አስተዳደር ላይ የሚደረገው ጫናና ማዕቀብ ፕሬዚደንት በሽር አል አሳድን እስከሚያንበረክክ ምን ያህል ጊዜ ይፈጅ ይሆን?- የሚለዉ የብዙዎች ጥያቄ ነው። የዶይቸ ቬለ ባልደረባ ያስፐር ባርንበርግ ያነጋገራቸው የጀርመኑ የውጭ ጉዳይ ፖለቲከኛ -ሮልፍ ሙንስኒሽ ጀርመን ከሩስያ ጋ ባላት ግንኙነት በመጠቀም ይህችው ሀገር ዓለም አቀፉ ማህበረ ሰብ በሶርያ መንግሥት ላይ የሚወስደውን ውሳኔ ትደግፍ ዘንድ እንድታግባባ ጠይቀዋል።
ገበያው ንጉሤ
ልደት አበበ
አርያም ተክሌ
ሸዋዬ ለገሰ