ቀጣዩ አጠቃላይ ምርጫና የፓርቲዎች ተሳትፎ ጉዳይ
ረቡዕ፣ መጋቢት 2 2001ማስታወቂያ
ቦርዱ ባለፉት ሁለት ምርጫዎች አልተሳተፉም ያላቸውን ፓርቲዎች ስም ዝርዝር አውጥቶ በህግ ሊወሰድ የሚገባውን ውሳኔ እንዲያሳልፍ ዝርዝሩን ለቦርዱ ከፍተኛ ኃላፊዎች ማቅረቡን ገልጾዋል። ይህ በሁለት ተከታታይ ምርጫዎች ያልተሳተፉ ፓርቲዎች ከቀጣዩ አጠቃላይ ምርጫ ተሳትፎ ሊታገዱ ይችላሉ የተባለበት ዜና ከያቅጣጫው የተለያየ አስተያየትና ተቃውሞ አስነስቶዋል። ይሁንና፡ በሁለት ተከታታይ ምርጫ ሲባል በሁለት አጠቃላይ ወይም በሁለት የማሟያ፡ ወይም በሁለት አጣቃላይና የማማያ ምርጫ መሆኑ በህጉ በግልጽ ያልተጠቀሰበት ጉዳይ ህጉን አሻሚ እንዳደረገው የህግ ባለሙያው አቶ ገብረጻዲቅ ተመስገን በተለይ ለዶይቸ ቬለ አስታውቀዋል። ታደሰ እንግዳው
AA/NM