1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የፖለቲካው ትኩሳት ሁከት እንዳያስነሳ ተሰግቷል

ቅዳሜ፣ መስከረም 13 2010

የኬንያ የተቃዋሚዎች ጥምረት ባለፈው ነሐሴ 2 ቀን 2009 ዓ.ም በሀገሪቱ በተካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ላይ ያቀረቡትን አቤቱታ የተመለከተው የኬንያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የምርጫው ውጤት ውድቅ እንዲደረግ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል፡፡ ፍርድ ቤቱ ድጋሚ ምርጫ በ60 ቀናት ውስጥ እንዲካሄድ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር፡፡

Kenia PK Raila Odinga zur Wahlniederlage
ምስል Reuters/T. Mukoya

የፖለቲካው ትኩሳት ሁከት እንዳያስነሳ ተሰግቷል

This browser does not support the audio element.

በራይላ ኦዲንጋ የሚመራው የተቃዋሚዎች ጥምረት የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ቢያወድስም ለጥቅምት 16 ቀን ከተቆረጠለት ድጋሚ ምርጫ በፊት በምርጫ አስፈጻሚው በኩል መስተካከል ይገባቸዋል ያላቸው ጉዳዮች ካልተደረጉ በምርጫው ላይሳተፍ እንደሚችል አስጠንቅቋል፡፡ በስልጣን ላይ ያሉት የፕሬዝዳንት አሁሩ ኬንያታ ቀንደኛ ተፎካካሪ ራይላ ኦዲንጋ ትላንት ከዶይቼ ቬለ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስም ይህንኑ ማስጠንቀቂያ ደግመውታል፡፡ ሳምንታዊው “ትኩረት በአፍሪቃ” ዝግጅታችን አወዛጋቢውን የኬንያን ምርጫ ጉዳይ በዋናነት ይመለከታል፡፡ የቶጎ መንግስት ህገመንግስቱን ለማሻሻል በመሞከሩ የተቀሰቀሰበትን ተቃውሞም በአጭሩ ይቃኛል፡፡ 

 

ገበያው ንጉሴ  

ተስፋለም ወልደየስ

 

 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW