1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ቃለ-ምልልስ ከአትሌት ፈይሳ ሌሊሳጋር

ዓርብ፣ ነሐሴ 20 2008

አትሌት ፈይሳ ለዶቼቬለ በሰጠው ቃለ ምልልስ ባደረገው እና በውሳኔው እንደሚኮራ ተናግሯል ።

Brasilien Olympische Spiele Rio 2016 21 08 - Marathon Feyisa Lilesa
ምስል Getty Images/AFP/O. Morin

[No title]

This browser does not support the audio element.

በርዮው ኦሎምፒክ በማራቶን የብር ሜዳልያ ካሸነፈ በኋላ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ተቃውሞውን በመግለጽ ወደ ሃገሩ ሳይመለስ የቀረው አትሌት ሌሊሳ ፈይሳ ኢትዮጵያውያን አድናቆታቸውን እየገለጹለት መሆኑን አስታወቀ ። ፈይሳ ለዶቼቬለ በሰጠው ቃለ ምልልስ ባደረገው እና በውሳኔው እንደሚኮራ ተናግሯል ። በውድድሩ ማብቂያ ላይ እጁን ወደ ላይ አውጥቶ በማጣመር በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ያለውን ተቃውሞ የገለጸው ፈይሳ ይህን በማድረጉ የመገደል ወይም የመታሰር ስጋት ስላለው ወደ ሃገሩ እንደማይመለስ በተወዳደረበት ዕለት በሰጠው መግለጫ ላይ ተናግሮ ነበር ።የኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ ፈይሳ በርዮ ባሳየው ተቃውሞ ምክንያት እንደማይቀጣ ነበር ያስታወቀው ። አትሌት ፈይሳን የለንደንዋ ዘጋቢያችን ሃና ደምሴ አነጋግራዋለች ።
ሃና ደምሴ
ኂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW