1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በለንደን በድርቅ ለተጎዱ የእርዳታ ስብስብ

ሰኞ፣ ታኅሣሥ 18 2008

እንግሊዝ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን የኪነጥበብ ባለሙያዎች ሀገር ዉስጥ በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች እርዳታ ማሰባሰቢያ የሚሆን ዝግጅት ታናንት አሰናድተዉ ነበር።

Äthiopien Mädchen beim Wasserholen
ምስል picture alliance/Ton Koene

[No title]

This browser does not support the audio element.

እኛዉ ለኛዉ በተሰኘዉ በዚህ ዝግጅትም እስከአምስት ሺህ የእንግሊዝ ፓዉንድ ሳይሰበሰብ እንዳልቀረ የዝግጅቱ አስተባባሪ ኮሚቴ ፀሐፊ እና የገንዘብ ማሰባሰቢያዉን መድረክ የመሩት አቶ ወንድወሰን አበበ ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል። የኪነጥበብ ባለሙያዎቹ በድርቅ የተጎዱት ገበሬዎች የእርዳታ ስንዴ ከመጠበቅ ይልቅ ዉኃን አዉጥተዉ ለእርሻቸዉ የሚያዉሉበት መሣሪያ ወይም ቴክኒዎሎጂ እንደሚሹ በመረዳታቸዉም አቅማቸዉ በፈቀደ የዉኃ ማዉጫ ማሽን ገዝተዉ በድርቁ ክፉኛ ለተጎዱ አካባቢዎች እንኳ ለመስጠት ማሰባቸዉንም አስረድተዋል። የገንዘብ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ኮሚቴዉን ፀሐፊ ሸዋዬ ለገሠ በአጭሩ ስለዝግጅቱ ጠይቃቸዋለች።

ሸዋዬ ለገሠ

እሸቴ በቀለ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW