1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በሐረሩ ግጭት የተጠረጠሩ 87 ሰዎች ታሰሩ 

ሰኞ፣ ጥር 18 2012

በተለያየ መንገድ በግጭቱ ተሳትፈዋል ተብለው በተጠረጠሩት በእነዚሁ ሰዎች ላይ ክስ ለመመስረት በዝግጅት ላይ መሆኑን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ለዶቼቬለ አስታውቋል። በግጭቱ የአንድ ሰው ሕይወት ማለፉን፤ ሰላማዊ ሰዎችና የፀጥታ ኃይሎች ጉዳት እንደደረሰባቸው እና ተሽከርካሪዎችም ተዘርፈው እንደነበር ፖሊስ ተናግሯል።

Hyänen Äthiopien
ምስል Reuters/T.Negeri

ፖሊስ ግጭቱን ለመከላከል ኃይል ተጠቅሟል አድሎም ፈጽሟል መባሉን አስተባብሏል

This browser does not support the audio element.

አንድ ሰው በሞተበት እና ሌሎች ሰባት ሰዎች በቆሰሉበት የዕለተ ጥምቀት የሐረር ግጭት እጃቸው አለበት ተብለው የተጠረጠሩ 87 ሰዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የሐረሪ ክልል ፖሊስ አስታወቀ። በተለያየ መንገድ በግጭቱ ተሳትፈዋል ተብለው በተጠረጠሩት በእነዚሁ ሰዎች ላይ ክስ ለመመስረት በዝግጅት ላይ መሆኑን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ለዶቼቬለ አስታውቋል። በግጭቱ የአንድ ሰው ሕይወት ማለፉን፤ ሰላማዊ ሰዎችና የፀጥታ ኃይሎች ጉዳት እንደደረሰባቸው እና ተሽከርካሪዎችም ተዘርፈው እንደነበር ፖሊስ ተናግሯል። ፖሊስ ግጭቱን ለመከላከል ኃይል ተጠቅሟል አድሎም ፈጽሟል መባሉን አስተባብሏል። 


መሳይ ተክሉ 


ኂሩት መለሰ
እሸቴ በቀለ
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW