በመተከል ዞን የቀጠለው የነዋሪዎች ቅሬታ
ሰኞ፣ መጋቢት 27 2013![Karte Äthiopien Metekel EN](https://static.dw.com/image/56261000_800.webp)
ማስታወቂያ
የቤኒሻንል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን በዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች በሰው እና ንብረት አሁንም ጥቃቶች እየደረሱ መሆንን ነዋሪዎች አስታውቀዋል። በአካባቢው የሚስተዋለውን የጸጥታ ችግር መንግሥት በዘላቂነት እንዲፈታም ጠይቀዋል። በድባጢ ወረዳም ሰሙኑን በርካታ ቤቶች መቃጠላቸውን ነዋሪዎች የተናገሩ ሲሆን የመጓጓዣ አገልግሎት ባለመኖሩ መቸገራውንም አክለዋል። ከነዋሪው ለተነሱት ቅሬታዎች ከአካባቢው አስቸኳይ ጊዜ አስተዳደር ወይም ኮማንድ ፖስት ስልክ ባለማንሳታቸው መረጃ ለማግኘት አልተቻለም።
ነጋሳ ደሳለኝ
ሸዋዬ ለገሠ
ኂሩት መለሰ