1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በምርጫ ቦርድ ውሳኔ ላይ የአፋር ክልል አስተያየት

ሐሙስ፣ መጋቢት 16 2013

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአፋር እና የሶማሌ ክልሎች በሚዋሰኑባቸው ስምንት ቀበሌዎች "ሊከፈቱ የነበሩትን 30 የምርጫ ጣቢያዎች በአካባቢው እንዳይቋቋሙ" መወሰኑን ትናንት አስታውቋል። "የምርጫ ጣቢያዎቹ በሶማሌ ክልል በሚገኙ ቀበሌዎች ስም ይፋ ተደርገዋል" የሚል አቤቱታ ያቀረበውን የአፋር ክልል ስለውሳኔው ምን ይላል?

Logo | National Election Board of Ethiopia
ምስል National Election Board of Ethiopia

በምርጫ ቦርድ ውሳኔ ላይ የአፋር ክልል አስተያየት

This browser does not support the audio element.

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአፋር እና የሶማሌ ክልሎች በሚዋሰኑባቸው ስምንት ቀበሌዎች "ሊከፈቱ የነበሩትን 30 የምርጫ ጣቢያዎች በአካባቢው እንዳይቋቋሙ" መወሰኑን ትናንት አስታውቋል። 
"ቦርዱ በ2007 ዓ.ም የተጠቀመበትን የመረጃ ዝርዝር ለ6ተኛው አገራዊ ምርጫ ቢጠቀምም፣ የምርጫ ጣቢያዎች የአስተዳደር ወሰኖችን የሚወስኑ መገለጫዎች ባይሆኑም ቦርዱ ምርጫ በምንም መልኩ የሰላም መደፍረስ ምክንያት እንዳይሆን በማሰብ" ከውሳኔው እንደደረሰ የትናንትናው መግለጫ ይጠቁማል። 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ "በአካባቢው የሚኖሩ እና የመራጮች ምዝገባ እና የድምጽ መስጠት ሂደት ውስጥ የሚሳተፉ ዜጎች በአቅራቢያቸው ባለ ሌላ ቀበሌ መመዝገብ እና ድምጻቸውን መስጠት" ይችላሉ ብሏል። ዮሐንስ ገብረእግዚዓብሔር "የምርጫ ጣቢያዎቹ በሶማሌ ክልል በሚገኙ ቀበሌዎች ስም ይፋ ተደርገዋል" የሚል አቤቱታ ያቀረበውን የአፋር ክልል ባለሥልጣናት ምላሽ በትናንትናው ውሳኔ ላይ ጠይቋል።

ዮሐንስ ገብረእግዚዓብሔር
ነጋሽ መሐመድ
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW