በሞቃዲሾ የቀጠለው ውጊያ2 ነሐሴ 2003ሰኞ፣ ነሐሴ 2 2003የሶማሊያው እሥላማዊ የዓመጽ ቡድን አሸባብ በሞቃዲሾ ይገኝ የነበረ ሃይሉን ቅዳሜ እለት ከስፍራው ማስወጣቱ ተገልጿል። ይሁንና በትናንትናው እለት በሞቃዲሾ በአሸባብ እና በመንግስት ወታደሮች መካከል ተኩስ ተከፍቶ እንደነበር ተሰምቷል።ማገናኛዉን ኮፒ አድርግሼክ አሊ ሞሀመድ ራጌ- የአሸባብ ቡድን ቃል አቀባይምስል APማስታወቂያየአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር አብዲዌሊ-ሞሐመድ-አሊም ከተማይቱ ሙሉ በሙሉ በአፍሪቃ ሕብረት ሰላም አስከባሪ ሃይል በሚደገፈው የሶማሊያ ጦር ቁጥጥር ስር መዋሏን ጠቅሰው አሸባብን ከምድረ ሶማሊያ ለማስወጣት ትግሉ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።ይህም ታጣቂዉ ቡድንም ስጋቱነቱ አሁንም እንዳልቀነሰ ያመለክታል እየተባለ ነዉ። ልደት አበበ ሸዋዬ ለገሠ