በሳዉድ አረቢያ የአዲስ ከተማ ግንባታ
ሐሙስ፣ ጥቅምት 16 2010ማስታወቂያ
26.5 ስኩየር ኪሎሜትር ስፋት የሚኖረው ይህ ከተማ የሚገነባው ለዓለም ሃገራት ሁሉ ቅርብ ነው በተባለው የሰሜናዊ ሳዉዲ ግዛት ግብጽ እና ዮርዳኖስን ተዋስኖ ነው፡፡ ከየትኛውም የዓለማችን ክፍል ኒዮም ተብሎ ወደ ተሰየመው ታላቅ ከተማ ለመድረስ ፈጀ ከተባለ 8 ሰዓት የአዉሮፕላን ጉዞ ብቻ ነው የሚወስደው፡፡
አልጋ ወራሹ እንዳሉት ሳዑዲ ዓረቢያም ባለፉት 40 ዓመታት ስትከተለው ከኖረችው የወግ አጥባቂ የእስልምና አስተምህሮ ተላቃ ለዘብተኛ የሚባለውን እስልምና ትከተላለች ፡፡ አዲስ የምትመሠረተው የኒዮም ከተማም አሁን ሥራ ላይ ባለው የሳዉዲ ሕግ እና ደንብ ተገዢ አትሆንም ፡፡ አክራሪነት እና ጽንፈኝነት ከእንግዲህ በሳዑዲ ዓረቢያ ቦታ እንደማይኖራቸውም ነው አልጋወራሽ መሀመድ ቢን ሰልማን ያስገነዘቡት፡፡ ስለሺ ሽብሩ ዝርዝር ዘገባ ከሪያድ ልኮልናል።
ስለሺ ሽብሩ
ሸዋዬ ለገሠ
አርያም ተክሌ