በሳዑዲ የሪትስ ካርልቶን ቅምጥል ሆቴል እስረኞች ይዞታ
ዓርብ፣ ታኅሣሥ 20 2010ማስታወቂያ
የሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት በታሳሪዎቹ ላይ የሚያከናውነው ምርመራ እጅግ ሚሥጥራዊ ቢኾንም አንዳንድ ሾልከው የወጡ ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት በቁጥጥር ስር ከዋሉት መካከል አንዱ ሜጀር ጄነራል ዓሊ አልቃታህኒ በደረሰባቸው የምርመራ ቁም ስቅል ሕይወታቸው መጥፋቱን እና ቤተሰቦቻቸውም የእስረኛውን አስክሬን ለመለየት እጅግ ተቸግረው እንደነበር ተገልጧል። ከእስረኞቹ መካከል ኢትዮጵያዊ ውስጥ በርካታ ኩባንያ ያላቸዉ ሼህ መሐመድ አላሙዲንም ይገኙበታል። የእስረኞቹ ወቅታዊ ኹኔታ ምን ይመስላል? ስቱዲዮ ከመግባቴ ቀደም ብሎ የሪያዱ ወኪላችን ስለሺ ሽብሩን በስልክ አነጋግሬው ነበር። ስለሺ ተለቀቁ ስለተባሉት እስረኞች በመግለጥ ይንደረደራል።
ስለሺ ሽብሩ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ነጋሽ መሐመድ