1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በስልጤ ዞን የአብያተ ክርስትያናት መቃጠል

ዓርብ፣ ሚያዝያ 21 2014

በስልጤ ዞን በሃይማኖት ተቋማት ላይ የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ እስከ ዐሥራ አምስት በሚደረሱ ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ። ነዋሪዎቹ አንዳሉት በቡድን የተሰባሰቡ ሰዎች በዞኑ በወራቤ ከተማ እና በሳንኩራ ወረዳ ላይ ቢያንስ ሦስት አብያተ ክርስትያናትን ማቃጠላቸውን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

Karte von Äthiopien
ምስል AP GraphicsBank/DW

እስከ 15 በሚደረሱ ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት ደርሷል

This browser does not support the audio element.

በስልጤ ዞን በሃይማኖት ተቋማት ላይ የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ እስከ ዐሥራ አምስት በሚደረሱ ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ። ነዋሪዎቹ አንዳሉት በቡድን የተሰባሰቡ ሰዎች በዞኑ በወራቤ ከተማ እና በሳንኩራ ወረዳ ላይ ቢያንስ ሦስት አብያተ ክርስትያናትን ማቃጠላቸውን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል። ዶቼ ቬለ (DW)  ያነጋገራቸው የስልጤ ዞን መስተዳድር የሥራ ኃላፊዎች በበኩላቸው ጉዳዩን በማጣራት ሂደት ላይ በመሆናችው ዝርዝር መረጃ መስጠት ባይችሉም ኅብረተሰቡን በማወያይት የማረጋጋት ሥራ በማከናወን ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል። 

ሸዋንግዛው ወጋየሁ

ማንተጋፍቶት ስለሺ

አዜብ ታደሰ
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW