1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

በቀድሞ የብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት ኃላፊና ሠራተኞች ላይ የቀረበው ክስ

ረቡዕ፣ ሚያዝያ 30 2011

የአዲስ አበባው ወኪላችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር እንደገለፀው በተጠርጣሪዎች ላይ የቀረበው ክስ ተመሳሳይነት አለው። ችሎቱ አቶ ጌታቸው አሰፋን ጨምሮ ፍርድ ቤት ያልቀረቡ አራት ተጠርጣሪዎች የፌደራል ፖሊስ ባሉበት መጥሪያ እንዲሰጣቸው አቃቤ ሕግ በጠየቀው መሠረት ነገ ለፖሊስ ትዕዛዝ ለመስጠት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

Symbolbild Justitia Justizia
ምስል፦ picture-alliance/dpa

አቃቤ ህግ በቀድሞ የብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት ኃላፊና ሠራተኞች ላይ የቀረበው ክስ

This browser does not support the audio element.

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ ልደታ ምድብ፤ አንደኛ ችሎት በቀድሞ የብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት ኃላፊና ሠራተኞች ላይ የቀረበውን ክስ ዛሬም ማድመጡን  ቀጥሏል። በዛሬው ችሎት የአንደኛውን ተከሳሽ የአቶ ጌታቸው አሰፋን ጨምሮ ከ5 ተኛ እስከ 19ኛ የተዘረዘሩ ተካሶችን ክስ አዳምጧል። ችሎቱን የተከታተለው የአዲስ አበባው ወኪላችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር በተጠርጣሪዎች ላይ የቀረበው ክስ ተመሳሳይነት እንዳለው ተናግሯል። ችሎቱ አቶ ጌታቸው አሰፋን ጨምሮ ፍርድ ቤት ያልቀረቡ አራት ተጠርጣሪዎች የፌደራል ፖሊስ ባሉበት መጥሪያ እንዲሰጣቸው አቃቤ ሕግ በጠየቀው መሠረት ነገ ችሎት ያልቀረቡትን ተከሳሾች በተመለከተ ለፖሊስ ትዕዛዝ ለመስጠት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። ስለ ዛሬው የፍርድ ቤት ውሎ ስቱድዮ ከመግባቴ በፊት ዬሐንስን በስልክ አነጋግሬው ነበር።

ዮሐስ ገብረ እግዚአብሔር 

ኂሩት መለሰ

ነጋሽ መሐመድ
 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW