1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

በቄለም ወለጋ ሶስት ሳምንታትን የተሻገረው የውሃና መብራት መቋረጥ

ቅዳሜ፣ ሚያዝያ 2 2013

በኦሮሚያ ክልል ቄለም ወለጋ ዞን ለሶስት ሳምንታት ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት ከትናንት ጀምሮ መመለሱን የአካባቢው ባለስልጣናት አረጋግጠዋል፡፡ በዞኑ ለሶስት ሳምንታት የዘለቀው የመብራት እና ውሃ መቋረጥ  የገጠመው ከጋምቤላ ክልል የሚመጣው የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር በታጣቂዎች በመቆረጡ ነው ተብሏል፡፡

Mendi city
ምስል፦ DW/N. Desalegn

በቄለም ወለጋ ዞን የመብራት እና ውኃ መቋረጥ

This browser does not support the audio element.

በኦሮሚያ ክልል ቄለም ወለጋ ዞን ለሶስት ሳምንታት ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት ከትናንት ጀምሮ መመለሱን የአካባቢው ባለስልጣናት አረጋግጠዋል፡፡
በዞኑ ለሶስት ሳምንታት የዘለቀው የመብራት እና ውሃ መቋረጥ  የገጠመው ከጋምቤላ ክልል የሚመጣው የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር በታጣቂዎች በመቆረጡ ነው ተብሏል፡፡
የዞኑ ፀጥታ እና አስተዳደር ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተሰማ ዋሪዮ በተለይ ለዶይቼ ቬለ እንዳሉት መስመሩ ለሶስት ሳምንታት ሳይጠገን ተቋርጦ የቆየው በፀጥታ ሃይሎች በአካባቢው ሳይደርሱ በመቆየታቸው ነው፡፡በአካባቢው ታጥቆ ይንቀሳቀሳል የተባለው ሸማቂ ቡድን የመብራት ኃይል ሰራተኞች ላይ እገታ መፈጸሙንም ባለስልጣናቱ ተናግረዋል፡፡
ስዩም ጌቱ 
ታምራት ዲንሳ
እሸቴ በቀለ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW